TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ኢትዮጵያ ውስጥ በየክልሉ የሚታዩ ሽኩቻዎች የሀገሪቱን አለመረጋጋት #እንዳያባብሱት ዓለም አቀፉ የቀውስ አጥኚ ቡድን አሳሰበ። ደቡብ ኢትዮጵያ ላይ የሲዳማ ሕዝብ መሪዎች ለጥያቄያቸው የፌደራል መንግሥትን #አዎንታዊ ምላሽ ካላገኙ ከፊል ራስገዝ አስተዳደርነትን በመጪው ሐምሌ አጋማሽ ለማወጅ መዘጋጀታቸውን አሳውቀዋል። ለተባለው ወሳኝ ቀን የሁለት ሳምንታት ዕድሜ ቢቀርም የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ሕዝበ ውሳኔ እንዲሰጥበት ቀን እንዳልቆረጡ እና ዝግጅትም እንዳላደረጉ ቡድኑ ይፋ ባደረገው ዝርዝር ዘገባ ጠቅሷል። ጉዳዩ በአግባቡ ካልተያዘ የሀገሪቱ ጥምር መሪ ፓርቲ የገጠመውን ቀውስ ሊያባብስ እንደሚችል ክራይስስ ግሩፕ አመልክቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና የግንባሩ መሪዎች ከሲዳማ ሕዝብ መሪዎች ጋር የሚግባቡበትን መንገድ እንዲፈልጉ እና ቆየት ብለውም ለሕዝበ ውሳኔው ቀን መቁረጥ እንደሚያስፈልግ አመልክቷል።

https://www.crisisgroup.org/africa/horn-africa/ethiopia/b146-time-ethiopia-bargain-sidama-over-statehood

Via #DW
🗞ቀን ሰኔ 27/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia