TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የራይድ አሽከርካሪዎች የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር #Ride
#RIDE

"ይህንን ደንብ አንቀበለውም፣ ከፍርድ ቤት እገዳ ለማስወጣት ሂደት ላይ ነን" የራይድ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ሳምራዊት

/ልዩ መረጃ-- ከኤልያስ ጋር/

የራይድ መስራች እና ስራ አስኪያጅ ሳምራዊትን የአ/አ ትራንስፖርት ቢሮ ይፋ ስላደረገው አዲሱ መመሪያ፦

"ሲጀመር የትራንስፖርት ቢሮው ይህን መመሪያ ማውጣት ይችላል ወይ የሚለው ላይ ጥያቄ አለ፣ ምክንያቱም እኛ የቴክኖሎጂ ድርጅት ስለሆንን የሚመለከተው የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ነው። በእኛ እምነት የትራንስፖርት ቢሮው ይህ ስልጣን የለውም። ሲቀጥል በRide ስር ከ 6,000 በላይ አባላት አሉ፣ የሚጎዱት እነዚህ ሰዎች ጭምር ናቸው። ይህ መመሪያ ሲወጣ እኛን ማሳተፍ ነበረበት። ሌላው ቀርቶ ረቂቁን እንኳን አላየነውም። በአጠቃላይ ይህንን ደንብ አንቀበለውም፣ ከፍርድ ቤት እገዳ ለማስወጣት ሂደት ላይ ነን። በሌለ infrastructure አንድን ድርጅት እዚህ ማድረስ ቀላል አልነበረም። ይህንን ሁሉ ስራ ሰርተን እዚህ ስንደርስ appreciate መደረግ ነበረብን። በትራንስፖርት ቢሮ የተደረገው ግን እኛን የሚቃረን ነው። እንደዚህ አይደረግም! ይህ ፈፅሞ መቆም ያለበት ነገር ነው። ይብቃ! ወጣቱ ይስራ! ሀገሪቱንም ያሳድግ! በዚህ አጋጣሚ ኢንጅነር ታከለ እና አቶ እንዳወቅ እየደገፉን ነው ያሉት። (የአ/አ ትራንስፖርት ቢሮው) ዶ/ር ሰለሞን ግን ትንሽ ቆም ብለው አስበው ከእኛ ጋር ቢሰሩ ጥሩ ነው። ብዙ ልምድ አለን። ምን አልባት ልምድ የላቸውም ብለው አስበው ከሆነ ተሳስተዋል።"

Via #ELIAS_MESERET
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#RIDE

"የምንሠራው በቴክኖሎጂ ዘርፍ ፍቃድ አውጥተን ነው። ፍቃድ እያለን ተጨማሪ ፍቃድ ማውጣት ለምን አስፈለገ?" የራይድ ሥራ አስኪያጅ ሳምራዊት ፍቅሩ

የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ቢሮ የኤሌክትሮኒክስ የታክሲ ስምሪትን በተመለከተ ያወጣው መመሪያ እንደ ራይድ ካሉ በቴክኖሎጂ ታግዘው የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶች ቅሬታ አስነስቷል።

በመመሪያው ከተካተቱ ነጥቦች አንዱ የሆነውና ሰሌዳቸው ኮድ 3 የሆኑ ተሽከርካሪዎች የኪራይ አገልግሎት ፍቃድ ካላወጡ በስተቀር የመጓጓዣ አገልግሎት መስጠት አይችሉም የሚለው የብዙዎች መነጋገሪያ ሆኖ ነበር።

በመመሪያው፤ በዘርፉ የታክሲ አገልግሎት ለመስጠት የሚሰማሩ አሽከርካሪዎች ሰሌዳቸውን ወደ ኮድ 1 እንዲቀይሩ እንዲሁም መኪናቸውን ቀለም እንዲቀቡ ተወስኗል። በተጨማሪም የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ አካላት በድርጅት መታቀፍ አለባቸው ተብሏል።

Via BBC

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-19
TIKVAH-ETHIOPIA
በራይድ እና ዛይ ራይድ መካከል ውዝግብ ተነስቷል! በራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት እና ዛይ ራይድ ሜትር ታክሲ መካከል ከንግድ ስም ባለቤትነት እና ከፈጠራ ባለቤትነት መብቶች ጋር በተያያዘ በተነሳው ውዝግብ ራይድ ባቀረበው አቤቱታ መሰረት በንግድ ውድድር እና ሸማቾች ጥበቃ ባለሥልጣን ምርመራ ተጀመረ። ከአራት ወራት በፊት ራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት የስያሜው የባለቤትነት መብት ይገባኛል በሚል ለኢትዮጵያ…
#RIDE #ZayRide

ራይድ ትራንፖርት የቅርብ ተወዳዳሪው ዛይ ራይድ ታክሲ ላይ አቅርቦት የነበረው ከስያሜ እና ከንግድ ምልክት ባለቤትነት ጋር የተያያዘ አቤቱታ ለክስ የሚያበቃ ምክንያት የለውም በማለት የንግድ ውድድር እና ሸማቾች ጥበቃ ባለሥልጣን ውድቅ አደረገው።

ሁለቱ ተቋማት የትራንስፖርት አገልግሎትን በቴክኖሎጂ በመደገፍ ተጠቃሚዎችን እና ደንበኞችን በስልክ መተግበሪያዎች በማገናኘት የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተሰማሩ ሲሆን ከንግድ ስያሜ እና ከባለቤትነት መብት ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ወዝግብ ውስጥ ገብተው እንደነበር የሚታወስ ነው።

ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FightCOVID19

- የአዲስ አበባ ከተማ ከተማ አሰተዳደር ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ ከሜድሮክ ኢትዮዽያ ኢትዮ አግሪሴፍ የተረከባቸውን 45 የደለቡ በሬዎች 'ማዕድ ማጋራት' በሚል ለአርባ ሰፈሮች በቄራዎች ድርጅት ጤናማነቱን ያረጋገጥ እርድ ተከናውኖ እንድሰራጭ በቄራዎች ድርጅት ግቢ ርክክብ ተደርጎል። የስጋ ስርጭቱን የአ.አ ቄራዎች ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ ሰይድ እንድሪስ እና ከአርባ ሰፈር በጎ ፈቃደኞች ወጣቶች ጋር በመተባበር ለመስራት ቃል ገብተዋል።

- አትሌት መሰረት ደፋር መገናኛ አካባቢ እያስገነባች ያለውን ባለ 12 ወለል ሕንጻ ኮቪድ-19ኝን ለመከላከል ለለይቶ ማቆያነት እንዲያገለግል አስረክባለች።

- ራይድ #RIDE የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት በሚደረገው ጥረት በተለያዩ የህክምና ተቋማት እያገለገሉ ለሚገኙ የጤና ባለሙያዎች እንዲሆን 50,000 የአፍ መሸፈኛ ማስኮችን ለኢትዮጵያ የህክምና ባለሙያዎች ማህበር አስረክቧል።

- ጋስት ሶላር መካኒክስ ኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) የያዛቸው ታካሚዎች አተነፋፈሳቸውን የሚያግዝ ቱቦ ወደ አየር ቧንቧቸው ሲገባ እንደ መከላከያ የሚያግዝ መሳሪያ ለጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እገዛ አድርጓል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot