TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ክብር ለጀግናው #የሀገር_መከላከያ_ሰራዊት! 7ኛው የመከላከያ ቀን! እንኳን አደረሳችሁ፤ እንኳን አደረሰን!

#ቲክቫህኢትዮጵያ #tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"የሰራዊቱን ስም #በማጠልሽተ የሚገኝ ምንም አይነት ቁምነገር የለም!"
.
.
መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ዩኒፎርም የለበሱና መለዮ አድርጎ በህዝብ መገልገያ ስፍራዎች ለሚገኙ ወታደሮች ከሁሉም ተገልጋይ በፊት ቅድሚያ በመስጠት፤ ለሞያውና #ለወታደሮቹ ያለንን #ክብር ማሳየት እንደሚኖርበት ጠቅላይ ሚስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ አሳሰቡ፡፡

ሚድያውን ጨምሮ አጠቃላይ የኪነ-ጥበብ ማህበረሰቡ መከላከያ ሰራዊቱ በሚፈለገው ደረጃ እንዲቀረፅና በህዝብ ዘንድ ያለው እምነት እንዲያድግ የማድረግ ሀላፊነት እንዳለውም ገልፀዋል፡፡

ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በ7ኛው የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ቀን በአል ላይ ባደረጉ ንግግር የኪነጥበብ ባለሞያዎች በሚሰሯቸው የኪነጥበብ ስራዎች የአገር መከላከያ ሰራዊትን በተመለከተ በጥንቃቄ ሊሰሩ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡

የሰራዊቱን ስም #በማጠልሸት የሚገኝም ምንም አይነት ቁምነገር እንደሌለም ጠቅላይ ሚንስትሩ አንስተዋል፡፡

#ሆሊውድ አገርን በውትድርና ማገልገል ትልቅ ሞያ እንደሆነ በማሳየት በኩል #ከፍተኛ ሚና የሚጫወት ሲሆን አሜሪካ በተሸነፈችባቸው አውደ ውጊያወችም ጭምር ወታደሮቿ የፈፀሙትን ገድል በማሳየት የወታደሮቻቸውን ጀግንነትና አገልጋይነት ለማጉላት ይሰራሉ፡፡

በአንፃሩ በአገራችን በአብዛኞቹ ፊልሞቻችን፣ ቀልዶቻችንና ፅሁፎቻችን የሚሳለው የወታደሮች እና የጦር አመራሮች ገፀባህሪ ቀረፃ #ጥንቃቄ_የጎደለው እንደሆነ መታዘብ እንደሚቻል ጠቅላይ ሚንስትሩ ጠቅሰዋል፡፡

ጠቅላይ ሚንስትሩ ለሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች መከላከያ ሰራዊት ነገ ህዝብ የመረጠው ፓርቲን ተቀብሎ የሚያስቀጥለው ሰራዊት በመሆኑ ከጅምላ ፍረጃ እና ሂስ ሊታቀቡ እንደሚገባ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ምንጭ፦ ena
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ👆

/ሚያዚያ 23/

ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ረቡዕ ምሽት #የTIKVAH_ETH ቤተሰብ አባላት ሲገቡ በተቋሙ ተማሪዎች እና በተማሪዎች ህብረት ልዩ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በፍቅር ተቀብለው አስተናግደዋቸዋል!! እራታቸውን እጉርሰው ማደሪያቸውን አመቻችተው ወንድምና እህቶቻቸውን በክብር አስተናግደዋቸዋል።

√ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ጋር ቀደም ብለን በተነጋገርነው መሰረት #የStopHateSpeech መድረክን ያካተተ ሌላ ትልቅ መድረክ እያዘጋጁ ስለነበር የውይይት መድረኮች ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፉ ሆኗል። ዩኒቨርሲቲውም በራሱ ፕሮግራም በትልቅ ዝግጅት ሊጠራ ስላሰበ የታቀዱ ስራዎች ለሌላ ጊዜ ተላልፏል።

እውነት የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ይለያሉ! #ፍቅርን#መተሳሰብን#አንድነትን ያሳዩን የቤተሰባችን አካል ናቸው። #ክብር ይገባችኃል!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተደረገ በሚገኘው ሰላማዊ ሰልፍ የተሰሙ መፈክሮች፦

√ከአጎራባች ህዝቦች ጋር ያለን #አብሮነታችን ተጠናክሮ ይቀጥላል!

√የክልልነት ጥያቄያችን በአስቸኳይ ይመለስ!

√የወላይታ ህዝብ በብዝሃነት ላይ የተመሰረተ አንድነትን #ይደግፋል!

√ሀገራዊ ለውጡ #ተጠናክሮ እንዲቀጥል የህግ የበላይነት ሊከበር ይገባል!!

√መንግስት በወላይታ ብሄር ተወላጆች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት #ሊያስቆም ይገባል።

√የደቡብ ክልል ምክር ቤት የህዝባችንን የክልል ጥያቄ አዳፍኖ መያዙን አጥብቀን #እንቃወማለን!

√በ1950ቹ የነበረው የወላይታ አውሮፕላን ማረፊያ #ይመልስልን!

√አሁን ያለው ሀገራዊ ለውጥ በምንም አይነት ሁኔታ #ሊደናቀፍ አይገባም!!

√እኛ የለውጥ #ደጋፊዎች ብቻ ሳንሆን የለውጥ #ባለቤቶች ነን!!

√ሀገር ለነበረው ወላይታ #ክልል መሆን አይከለከልም!!

√ስራ ወዳድነት #ክብር እንጂ ውርደት አይደለም!

√ወላይታ በሞግዚቶች መመራት በቃው! ጋሞ፣ ጎፋ፣ ሲዳማ፣ ዳውሮ የወላይታ ወንድም ሕዝቦች ናቸው!

√ኢትዮጵያዊነት ፀጋ እንጂ ኩነኔ ሊሆን አይገባም!

√የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለወላይታ!


በአሁን ሰዓት በወላይታ ሶዶ ስታዲየም ብዙ ሺ ሰዎች በተገኙበት የማጠቃለያ ፕሮግራም እየተካሄደ እንደሆነ ለመስማት ችለናል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጄነራል #ሰዓረ_መኮንን ህይወታቸው ከማለፉ ከሰዓታት በፊት ከኢ/ር ታከለ ኡማ ጋር ችግኝ በተከሉበት የቦሌ ሩዋንዳ አከባቢ የመታሰቢያ ፓርክ ሊሰራላቸው ነው፡፡ በመታሰቢያ ፓርኩ ውስጥ የጀነራሉን #ክብር በሚመጥን መልኩ የማስታወሻ ሀውልት የሚሰራላቸው ይሆናል፡፡ ችግኙን ከተከሉበት ከቦሌ ሩዋንዳ ድልድይ ጀምሮ እስከ አትላስ ሆቴል ያለው ጎዳናም በስማቸው እንዲሰየም የከተማ አስተዳደሩ ወስኗል፡፡ በከተማው የሚገኙ አርክቴክቶችና የአርት ስኩል ባለሙያዎችም የጄነራል ሰዓረን የማስታወሻ ሀውልት ንድፍ ሰርተው አጠናቀዋል፡፡ የመታሰቢያ ፓርኩን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በባለቤትነት የሚያስገነባው ይሆናል፡፡

ምንጭ፦ የከንቲባ ፅ/ቤት
🗞ቀን ሰኔ 29/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#ድሬዳዋ

" ለከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የምንሰጠው #ክብር ትልቅ ነው " - ድሬዳዋ

በመላው ኢትዮጵያ ካሉ ከተሞች ለእንግድነትም ሆነ እዛው በከተማዋ እየሰሩ ለመኖር አስተማማኝ የሰላም እና ፀጥታ ደህንነት ካለባቸው ከተሞች አንዷ ድሬዳዋ ናት።

ከተማይቱ በአንድ ወቅት አጋጥሟት ከነበረው የፀጥታ መንገጫገጭ ከወጣች በኃላ ላለፉት ዓመታት እጅግ አስተማማኝ ደህንነቷና ሰላሟን አስጠብቃ ትገኛለች።

በማታም ሆነ በቀን በከተማዋ ውስጥ ለመንቀሳቀስ እንዲሁም ሰርቶ ለመግባት ያማታሰጋ ሆና ተሰርታለች።

ከዚህ ባለፈም ፤ #የኢትዮጵያ የጀርባ አጥንት በሆነው ዋና መንገድ ላይ በመገኘቷ በርካታ አሸክርካሪዎች በየዕለቱ ታስተናግዳለች።

ብዙ ርቀት በአስቸጋሪ የአየር ፀባይ የሚጓዙ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ደህንነታቸው እንዲጠበቅና ፤ በሌሎች ቦታዎች ላይ የሚስተዋለው የተንዛዛ የትራፊክ ፖሊስ ጭቅጭቅ እንዳይኖርም እያደረገች ትገኛለች።

የድሬዳዋ ከተማ የትራፊክ ፖሊስም ረጅም መንገድ በረሃና አስቸጋሪ የአየር ንብረት በመቋቋም የሀገሪቱን ገቢ እና ወጪ ንግድ ለሚያፋጥኑ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የሚሰጠው #ክብር ትልቅ መሆኑን የሚገልፅ ሲሆን ማንኛውም አሽከርካሪ በከተማው ውስጥ ሆኖ ችግር ከገጠመው ለማስተካከል ዘውትር ዝግጁ ነኝ ብሏል።

#ቪድዮ፦ ከወር በፊት የከተማይቱ አመራሮች ረጅም ርቀት ተጉዘው ድሬዳዋ ከተማ የደረሱ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎችን ለማክበር የታሸገ ውሃ ሲሰጧቸው የሚያሳይ ነው።

@tikvahethiopia