TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሰበር ዜና‼️

“አባ ቶርቤ” በሚል መጠሪያ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በድብቅ በመንቀሳቀስ ሰዎችን ሲገድሉና ሲያስገድሉ የነበሩ ተጠርጣሪዎች #በቁጥጥር ስር ዋሉ።

የኦሮሚያ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ እንዳስታወቀው፥ ብሄራዊ የመረጃ እና የደህንነት አገልግሎት ባደረገው ክትትል በዛሬው እለት ስድስት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ተጠርጣሪዎቹ “አባ ቶርቤ” (ባለሳምንት) በሚል መጠሪያ በመደራጀት ሰላማዊ ዜጎችን፣ የመንግስት ባለስልጣናት እና የፀጥታ ሀይሎችን #ሲገድሉ እና #ሲያስገድሉ ነበር በሚል ነው ተጠርረው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

የተጠርጣሪዎቹን ማንነትና ዝርዝር መረጃ እንደደረሰው ይፋ እንደሚያደርግም አስታውቋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አባ ቶርቤ‼️በኦሮሚያ ክልል “አባ ቶርቤ” (ባለ ሳምንት) በሚል ስም #በህቡዕ ተደራጅቶ የመንግሥት ባለሥልጣናትን፣ ጸጥታ ሃይል አባላትንና ንጹሃን ዜጎችን ሲገድል የቆየው ቡድን ውስጥ አባል የሆኑ ግለሰቦች እየተያዙ ይገኛሉ፡፡ ትላንት ከተያዙት መካከል ጋዲሳ ነጋሳ፣ መርጋ ተፈራ እና አኒሳ ጌታቸዉ #በነቀምት፣ ደምቢ ዶሎ፣ ነጆ እና ሰሜን ሸዋ ሰዎችን #ሲገድሉና #ሲያስገድሉ የነበሩ ሲሆኑ አዲስ አበባም #ባለሥልጣናትን የመግደል #ዕቅድ ነበራቸው፡፡ ተጠርጣዎቹ በምዕራብ ኦሮሚያ ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ሃይሎች ጋር ግንኙነት አላቸው ተብሏል፡፡

Via~wazemaradio
@tsegabwolde @tikvahethiopia