TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ደቡብ ሱዳን ሟቾችን እየደበቀች ነው?

የደቡብ ሱዳን 2 ዶክተሮች ሀገራቸው የኮቪድ-19 ሞቶችን ሪፖርት እያደረገች አይደለም ብለዋል!

ሁለት (2) በኮቪድ-19 ላይ የሚሰሩ ዶክተሮች የሀገሪቱ መንግስት በኮቪድ-19 የሚሞቱ ሰዎችን ሪፖርት እያደረገ አይደለም ሲሉ ለ #SSNN ተናግረዋል።

አንደኛው የህክምና ዶክተር በጁባ ወታደራዊ ሆስፒታል በኮቪድ-19 ላይ የሚሰሩ ሲሆን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ሳይቀሩ በኮሮና ቫይረስ ሞተዋል ፤ የሀገሪቱ መንግስት ግን ሪፖርት አላደረገም ብለዋል።

ሌላኛው ዶክተር 'የደህንነትና የፀጥታ አካላት' ስለመንግስት የስራ ኃላፊዎች የኮቪድ-19 ሞት ለየትኛውም ሚዲያ እንዳትናገሩ ብለውናል ሲል ለSSNN ገልፀዋል ፤ በሀገሪቱ የመጀመሪያው ሞት የተመዘገበው ሚያዚያ ወር ነው የቀድሞው የደቡብ ሱዳን የፍትህ ሚኒስትር ፓውሊኒሆ ዋናዊላ ሁናጎ ሲሞት ነገር ግን መንግስት ሪፖርት አላደረገም ሲሉ ለ #SSNN ተናግረዋል።

የደቡብ ሱዳን መንግስት ዛሬ በሀገሪቱ የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ሞት መመዝገቡን አሳውቋል። ዝርዝር መረጃዎችን ግን አልሰጠም።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በደቡብ ሱዳን የመጀመሪያው ሞት ተመዘገበ! በደቡብ ሱዳን ከኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ጋር በተገናኘ የመጀመሪያው #ሞት መመዝገቡ ተሰምቷል። ከዚህ በተጨማሪ በሀገሪቱ በአንድ ቀን 28 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 231 ደርሰዋል። @tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#SouthSudan

የደቡብ ሱዳን ጤና ሚኒስቴር ዛሬ በሀገሪቱ የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ሞት በይፋ መመዝገቡን ሪፖርት ከማድረግ ውጭ ስለሟቹ ዝርዝር መረጃ አልሰጠም።

#SSNN ግን ሟቹ የቀድሞ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥ የሆኑት ብርጋዴር ጄነራል ጆን ማዴንግ ጋታዴል ናቸው ሲል ዘግቧል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#SouthSudan

የደቡብ ሱዳን የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር ሚካኤል ማኩዪና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ማርቲን ኤሊያ ሎሞሮ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ከተረጋገጠ ከፍተኛ ባለስልጣናት መካከል እንደሚገኙበት #SSNN ይፋ አድርጓል።

2ቱም ሚኒስትሮች ባለፈው ወር ናሙና ለመስጠት ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተው ነበር የተባለ ሲሆን በዚህ ወር ግን ምርመራ ሲደረግላቸው ሁለቱም በቫይረሱ መያዛቸው መረጋገጡን #SSNN ስማቸው ካልተገለፀ 'የኮቪድ-19 ታስክ ፎርስ' አባል መረጃ ማግኘቱን ገልጿል።

ሌላ አንድ ስማቸው ያልተገለፀ ምንጭ ደግሞ ሁለቱም (2) ሚኒስትሮች ጤናቸው ጥሩ የሚባል ደረጃ ላይ እንደሚገኝ እና ምልክት እንደማይታይባቸው አሳውቀዋል ሲል #SSNN ዘግቧል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia