TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#DrMikeRyan

የዓለም ጤና ድርጅት የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ተጠቂዎች ቁጥር እየቀነሰባቸው ባሉ ሀገራት ቫይረሱን ለመከላከል የተጣሉ እገዳዎች በቶሎ የሚነሱ ከሆነ ወረርሽኙ ለሁለተኛ ጊዜ ወረርሽኙ ከፍተኛ ደረጃ ይደርሳል ሲል #አስጠንቅቋል፡፡

የድርጅቱ የአስቸኳይ ጊዜ ጉዳዮች ኃላፊ ዶ/ር ማይክ ርያን አለም በመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ሞገድ ውስጥ ነች፤ ምንም እንኳን በብዙ ሀገራት በቫይረሱ የመያዝ መጠን እየቀነሰ ቢሆንም በማእከላዊና በደቡብ አሜሪካ እየጨመረ ነው ብለዋል፡፡

እንደ ዶክተር ማይክ ርያን ከሆነ ወረርሽኞች ሁሌም ወቅታዊ ናቸው ፤ በዚህ አመት የመጀመሪያው ሞገድ ያቆመባቸው ሀገራት እንደገና ይመለሳል ብለዋል፡፡ ቫይረሱን ለመከላከል የተጣሉ ክልከላዎች ቶሎ የሚነሱ ከሆነ ቫይረሱ በፍጥነት ሊስፋፋ የሚችልበት እድል እንዳለ ገልጸዋል - #AlAin

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia