TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጎንደር‼️

በጎንደር በተከሰተው ግጭት ዙሪያ የሚወጡ #የተምታቱ መረጃዎች ለውጡን የሚጎዱ መሆናቸውን የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ።

በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ የሰጡት የኢፌዴሪ ጦር ሃይሎች ምክትል ኤታ ማጆር ሹምና የዘመቻ መምሪያ ሀላፊ ጀነራል #ብርሃኑ_ጁላ እንደተናገሩት በጎንደር በተከሰተው ግጭት ዙሪያ የተምታቱ መግለጫዎች እየወጡ ነው፡፡

ስለ ክስተቱ ተገቢው የማጣራት ስራ ሊሰራ ይገባል፡፡ ተገቢው #የማጣራት ስራ ሳይሰራ መከላከያው ህዝብን ገድሏል ተብሎ እየተሰጡ ያሉ መግለጫዎችና በማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጩ ያሉ መረጃዎች ተገቢነት የጎደላቸው ናቸው፤ የተጀመረውን ለውጥም የሚጎዳ ነው ብለዋል፡፡

ምንጭ፦ EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia