TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የሼክ አላሙዲን ነገር⁉️

"ቢቢሲ ዛሬ በለቀቀው ዘጋቢ ፊልም እነ ሼክ አላሙዲንን ከሳዑዲ ልዑላውያን ጋር ደምሮ ያሳረዉ የሳዑዲ መንግስት በታሳሪዎቹ ላይ የከፋ #ድብደባ እና #ማሰቃየት እንዲሁም #ግድያ እየፈፀመ ነዉ ሲል ዘጋቢ ፊልም ሰርቷል። ከሟቾች ዉስጥ ጄኔራል አሊ አልካታኒ አንዱ ናቸዉ። ሞሐመድ ቢን ሰልማን የሚባለዉ እና ፖለቲካዊ አመለካከቱ ሊበራል ነዉ ተብሎ ሲወደስ የነበረዉ በቅጽል ስሙ ኤም ቢ ኤስ የተባለዉ የሳዑዲ አልጋወራሽ በእርሱ ትዕዛዝ የታሰሩ ባለሀብቶችና ንጉሣውያን ቤተሰቦች በድብደባ ምክንያት የደረሰባቸውን ጉዳት በሌላ ሆስፒታል እንዳይታከሙ በሪትዝ ሆቴል ተንቀሳቃሽ ሆስፒታል ከፍቷል። ይህ ዘገባ የተሰራዉ በቅርቡ ቱርክ በሚገኘዉ በሳዑዲ አረቢያ ቆንስላ
በጋዜጠኛ #ጀማል_ካሾጊ ላይ የተፈፀመዉን ግድያ ጋር ተንተርሶ ነዉ። አላሙዲን ምን ሁኔታ ላይ ይገኛሉ? የኢትዮጵያ መንግስት ያለዉ መረጃ
ምንድነዉ? ከአላሙዲን ጋር ሲበሉ ሲጠጡ ሲያተርፉ ሲነግዱ ያዙን ልቀቁን ሲሉ የነበሩ የት አሉ ? አላሙዲ ታሰረ አልታሰረ ጉዳያቸዉ አይደለም። ነገር ግን በእርሳቸዉ እርዳታ ህክምና ላገኙ እርዳታ ለተደረገላቸው ጥቂት ኢትዮጵያውያን ቤት ተሰርቶ ለተሰጣቸዉ ድሆች ስንል የመሐመድ ቢን ሰልማን ሰለባ እንዲሆኑ አንሻም። በሙስና የሚጠየቁ ከሆነም በፍርድ ቤት በአግባቡ መሆን አለበት ከጥላሁን ገሠሠ እስከ ካሚላት ላደረጉት በጎ ምግባር እናመሰግናለን።"

©Hailemelekot Agizew
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#US አሜሪካ በአስከፊው ጓንታናሞ ቤይ እስር ቤት አስራው የነበረችውን አልጄሪያዊ ወደ ሀገሩ መለሰች። አሜሪካ በሀገሯ ውስጥ የ "ቦምብ ጥቃት ለማድረስ አቅደሃል" ብላ ለ20 ዓመታት ገደማ ያሰረችውን ሱፊያን ቡርሃሚ የተባለ አልጄሪያው ወደ ሀገሩ እንዲመለስ አድርጌዋለሁ ብላለች። በአስከፊው ጓንታናሞ ቤይ እስር ቤት አሜሪካ አስራ ያቆየችው እና አሁን መልሸዋለሁ ያለችው አልጄሪያዊ በፈረንጆቹ 2002 ፓኪስታን…
#አሜሪካ

አሜሪካ ያለ አንዳች ፍርድ ለ20 ዓመታት በ " ጓንታናሞ ቤይ " በሚገኘው እስር ቤት አስራ የቆየቻቸውን ሁለት ፓኪስታናውያን ወንድማማቾችን ከእስር ስለመልቀቋ ተነግሯል።

ጓንታናሞ ቤይ ውስጥ በሚገኘው የአሜሪካ ወታደራዊ እርስ ቤት ውስጥ ለ20 ዓመታት ያህል ታስረው የቆዩት ሁለቱ ፓኪስታናውያን ወንድማማቾች ምንም ክስ ሳይቀርብባቸው ነው የተለቀቁት።

አብዱል እና ሞሐመድ አህመድ ራባኒ ፓኪስታን " ካራቺ " ውስጥ ተይዘው ከአገራቸው የተወሰዱት በአውሮፓውያኑ በ2002 ነበር።

የአሜሪካ መከላከያ መ/ቤት አብዱል ራባኒ የተባለው ግለሰብ የ " አልቃኢዳን የመደበቂያ ቤት ያስተዳድራል " እንዲሁም ወንድሙ " የቡድኑ መሪዎችን ጉዞ እና ገንዘብን ይመራል " ብሎ ነበር።

ወንድማማቾቹ ወደ ጓንታናሞ ከመሸጋገራቸው በፊት ከአገራቸው ውጪ በሲአይኤ (CIA) መኮንኖች #ማሰቃየት እንደተፈጸመባቸው ገልጸዋል።

ሁለቱ ፓኪስታናውያን ከአስፈሪው ወታደራዊው እስር ቤት ከተለቀቁ በኋላ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል ተብሏል።

ጓንታናሞ ኩባ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን የአሜሪካ ባሕር ኃይል ሰፈር ከመስከረም 11 የሽብር ጥቃት በኋላ ተጠርጣሪዎችን ለማቆያነት በቀድሞ ፕሬዝዳንት ጆርጅ ቡሽ የተቋቋመው ነው።

ካምፑ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት አሜሪካ ካካሄደችው " ፀረ ሽብር ጦርነት " ጋር በያያዘ ከተፈጸሙ መጥፎ ድርጊቶች ጋር ስሙ ይነሳል።

በተለይ ተጠርጣሪዎች በምርመራ ጊዜ #ከባድ_ሰቆቃ እንደተፈጸመባቸው እና ያለፍርድ ለረጅም ጊዜ በእስር እንዲቆዩ መደረጋቸው ይነገራል።

ከ20 ዓመት በፊት በጓንታናሞ ውስጥ 680 አስረኞች የነበሩት ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ግን 32 እስረኞች ብቻ የሚገኙበታል።

#BBC

@tikvahethiopia