TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሜጄር ጄኔራል ክንፈ ዳኛው‼️

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 10ኛ የወንጀል ችሎት ሜጄር ጄኔራል #ክንፈ_ዳኘውን ጨምሮ የስድስት ተጠርጣሪዎችን ጉዳይ እየተመለከተ ነው።

ሜጄር ጄኔራል ክንፈ ዳኘው ገቢዬ በጡረታ ማገኘው 4 ሺህ ብር ብቻ በመሆኑ መንግስት ጠበቃ ያቁምልኝ ማለታቸውን ተከትሎ በዚህ ጥያቄያቸው ላይ ፖሊስ ተቃውሞውን ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል።

የፌደራል ፀረ ሙስና ስነ ምግባር ኮሚሽን ያስመዘገቡትን ሀብት እና እስከ ህዳር 5 ቀን 2011 ዓመተ ምህረት ድረስ ስሙ ባልተጠቀሰ ባንክ ውስጥ ያላቸው ተቀማጭን በማስረጃነት አቅርቧል።

ጋዜጠኛ ፍጹም የሽጥላ ባቀረበችው ጥያቄ መሰረት የመንግስት ተከላካይ ጠበቃ ቆሞላታል።

ፖሊስ ለፍርድ ቤት እንዳብራራው፥ ጋዜጠኛ ፍጹም፤ ፍፁም ኢንተርቴይንመንት ለተባለ ድርጅት ባልተገባ ስፖንሰርሺፕ ብር 954 ሺህ 770 ብር የህዝብ ገንዘብ መውሰዷን ገልጿል።

በገንዘቡም የንግድ ድርጅት ከፍተው አፍርተዋል ያፈሩትንም ሀብት ሰውረዋል በሚል መጠርጠሯን ፖሊስ ለፍርድ ቤት አስረድቷል።

ፍርድ ቤቱ በአሁኑ ወቅትም የሌሎች ተጠርጣሪዎችን ጉዳይ እየተመለከተ ይገኛል።

ምንጭ ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኛው‼️

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 10ኛ የወንጀል ችሎት የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር ሜጄር ጀኔራል #ክንፈ_ዳኘውን ጉዳይ በመመልከት ላይ ይገኛል።

ፍርድ ቤቱ ሜጄር ጀኔራል ክንፈ ዳኘው መንግስት የመደበላቸውን መከላከያ ጠበቃ በማንሳት በራሳቸው ጠበቃ እንዲያቆሙ ባለፈው አርብ ብይን መስጠቱ ይታወሳል።

በዚህም መሰረት ሜጄር ጀኔራል ክንፈ ዳኘው በራሳቸው የግል ጠበቃ አቁመዋል።

ሆኖም ተጠርጣሪው ከግል ጠበቃቸው ጋር መገናኘት እንዳልቻሉ እና መርማሪ ባለበት የተገናኘን በመሆኑ ሚስጥር ማውራት አልቻልንምና ለመወያየት ጊዜ ይሰጠኝ ብለው በመጠየቃቸው ፍርድ ቤቱ ሌሎች ጉዳዮች እስከሚታዩ ድረስ ብሎ እንዲወያዩ ፈቅዷል።

የኢትዮ ቴሌኮም የሴኪዩሪቲ ዲቪዥን ኃላፊ የነበሩት ኮለኔል #ጉደታ_ኦላናም ዛሬ በዚሁ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

ያልታወቀ ሀብት በማካበት እና በተጠረጠሩበት በዚህ ወንጀል እና በሌሎች የሙስና ወንጀሎች ላይ የሚደረግ ምርመራን በማደናቀፍ ወንጀል ተጠርጥረው ነው ፍርድ ቤት የቀረቡት።

ተጠርጣሪው ጠበቃ ለማቆም የገቢ አቅም የለኝም በማለታቸውም መንግስት ጠበቃ አቁሞላቸው ጉዳዩን ለማየት ፍርድ ቤቱ ለህዳር 13 ቀን 2011 ቀጠሮ ሰጥቷል።

በሌላ በኩል መርማሪ ፖሊስ የቀድሞው የብሄራዊ መረጃና ደህንነት የስራ ባልደረባ አቶ #ተስፋዬ_ኡርጌን በተጨማሪነት በሰብዓዊ መብት
ጥሰትና በሙስና ወንጀል ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።

አቶ ተስፋዬ ኡርጌ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 10ኛ የወንጀል ችሎት ቀርበዋል።

መርማሪ ፖሊስም የቀድሞውን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት የስራ ባልደረባ በተጨማሪነት በሰብዓዊ መብት ጥሰትና በሙስና ወንጀል ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር እንዳዋላቸው ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።

አቶ ተስፋዬ የደህንነት መምሪያ ሀላፊ ሆነው ሲሰሩ ሰዎችን በሽብር ተጠርጥራችኋል በሚል በስውር እስር ቤት በማሰርና በማሰቃየት፥ እርቃናቸውን በካቴና አስረው ቆሻሻ ገንዳ ውስጥ በማቆየት፣ ግለሰቦችን ባልተገባ መልኩ ለሽብር መልምለው ወደ ኤርትራ በመላክ እንደጠረጠራቸው ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ገልጿል።

ከዚህ ባለፈም በሽብር ከተጠረጠሩ ሰዎች ላይ ገንዘብ በመቀበል እና በሀዋላ ከተጠርጣሪዎች ላይ ህገ ወጥ ገንዘብ በመቀበል በሰብዓዊ መብት ጥሰትና በሙስና ወንጀል ጠርጥሬያቸዋለሁም ብሏል መርማሪ ፖሊስ።

ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅም 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀን ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

አቶ ተስፋዬ በሰጡት ምላሽ እርሳቸው የተጠረጠሩበት ጉዳይ በግልጽና በተናጠል እንዳልቀረበ በመግለጽ፥ እርሳቸውን ለመያዝ በቂና ዝርዝር ጉዳይ አለመኖሩን አስረድተዋል።

በተጨማሪም ሀብት የመፍጠር ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው ሃብት ማፍራታቸውንና ለአራት ወራት ፍርድ ቤት እየተመላለሱ መሆኑን በመጥቀስ፥ ሃብት ከማፍራት ጋር ተያይዞ ሀምሌ 5 ቀን 2010 ዓ.ም ቤታቸው መበርበሩንና ምርመራው በወቅቱ ማለቅ ነበረበት ብለዋል።

አሁን ላይ መርማሪ ፖሊስ የጠየቀው ተጨማሪ ጊዜም ሊሰጥ አይገባም በማለት ተቃውመዋል።

ችሎቱም አቶ ተስፋዬ በተጨማሪነት የተጠረጠሩበት ወንጀል በተብራራ መልኩ እንዲቀርብና ፖሊስ የጠየቀውን 14 ቀን #በመፍቀድ ለህዳር 24 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ምንጭ:- ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሜጀር ጀኔራል ክንፈ ዳኘው‼️

መርማሪ ፖሊስ ሜጀር ጀኔራል #ክንፈ_ዳኘውን በተመለከተ እስካሁን በሰራው የምርመራ ስራ አገኘኋቸው ያላቸውን ተጨማሪ ማስረጃዎችን ለፍርድ ቤት አቅርቧል።

ፖሊስ በዛሬው እለት ግለሰቡን በተመለከተ ከዚህ ቀደም ካቀረባቸው ማስረጃዎች በተጨማሪነት አዳዲስ ያላቻውን ነው ያቀረበው።

በዚህም በ2003 ዓ.ም በሜቴክ ስም ከተለያዩ ተረፈ ምርቶች ወይም ቆሻሻ የናፍጣ ነዳጅ ማምረቻ ፋብሪካን ለመግዛት ያለ ምንም ጨረታ ኬዲቪ ከተባለ የጀርመን ኩባንያ ጋር የ8 ሚሊየን ዩሮ ግዥ ውል በመፈጸም፥ ከዚህ ውስጥ 4 ሚሊየን 800 ሺህ ዩሮ ለኩባንያው
እንዲፈጸም በማድረግ እንደጠረጠራቸውና ከዚህ ጋር የተያያዙ በርካታ የሰነድ ማስረጃዎች መሰብሰቡን ጠቅሷል።

በተጠቀሰው ዓ.ም ሜቴክ ከኢኳቶሪያል ቢዝነስ ግሩፕ ጋር በመመሳጠር ከመመሪያ ውጭና ያለ ግዥ ፍላጎት የ22 ሚሊየን ብር ዋጋ ያላቸው 20 ተሽከርካሪዎች ግዥ እንዲፈጸምና ለተፈጸመው ግዥ ክፍያ እንዲፈጸም ለኮርፖሬት ኢንቨስትመንትና ፋይናንስ ማኔጅመንት አላግባብ ትዕዛዝ ሰጥተዋል በሚል የተጠረጠሩ፤ ተጠርጣሪው የሜቴክ ዋና ዳይሬክተር በነበሩበት ወቅት ኮርፖሬሽኑ ከተቋቋመበት አላማ ውጭ ስልጣናቸውን አላግባብ በመጠቀም #የኢምፔሪያል_ሆቴል ግዥ በ71 ሚሊየን ብር ከአክሰስ ሪል ስቴት ባለቤት አቶ ኤርሚያስ አመልጋ እንዲፈጸም በማድረግ፣ ባለ አምስት
ወለል ህንጻ በ15 ሚሊየን ብር ከያማሉክ ኢንተርናሽናል ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ግዥ እንዲፈጸም በማድረግና በማፅደቅ።

ባለ አራት ወለል ህንጻ በ24 ሚሊየን 56 ሺህ ብር ከአቶ አለሙ ደምሴ ግዥ እንዲፈጸም በማድረግ፣ ባለ አንድ ወለል የመኖሪያ ህንጻ በ5 ሚሊየን 700 ሺህ ብር ከአቶ ጌታቸው አቃኔ ግዥ እንዲፈጸም በማድረግ፣ ባለ ሁለት ወለል ህንጻ የመኖሪያ ህንጻ በ8 ሚሊየን 700 ሺህ ብር ከአቶ ሙላቱ ረዳ እና ከወይዘሮ ሄለን በለጠ ግዥ እንዲፈጸም በማድረግ እና ባለ ሶስት ወለል ህንጻ በ12 ሚሊየን 700 ሺህ ብር ከጌት ፋም ሃላፊነቱ የተወሰነ ማህበር ባለቤት አቶ ጌታሁን በሻህ ግዥ እንዲፈጸም ትዕዛዝ በመስጠት፥ ውሎችን በማፅደቅ ግዥ እንዲፈጸምና የህዝብና የመንግስት ሃብት እንዲባክን በማድረግ ከቆሻሻ የጄት ነዳጅ ማምረቻ ፋብሪካ ግንባታ ከግዥ መመሪያ ውጭ ጨረታ ሳይወጣ ኢ ቪ ጂቲዲሲ ዌስት ቱ ኢነርጅ ከተባለ የአሜሪካ ኩባንያ ጋር የ347 ሚሊየን 948 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ውል ስምምነት ኮሎኔል ሙሉ ወልደገብርኤል 2005 ዓ.ም ላይ ውል እንዲዋዋል በማድረግና ውሉን በማፅደቅ፣ የውጭ ምንዛሪ እንዲፈቀድ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኤል ሲ በማስከፈት፣ ለባንክ አገልግሎት የሚውል ክፍያ 5 ሚሊየን 616 ሺህ 648 ብር ከ60 ሳንቲም የግንባታ ስራ ውል ስምምነት ከተፈጸመ በኋላ ውሉ ባልታወቀ ምክንያት በመቋረጡና ስራው ሳይሰራ ያለ አግባብ የመንግስት ገንዘብ እንዲባክን በማድረግ ለታላቁ የህዳሴ ግድብ የተከለለ ቦታ ላይ የሚገኘውን ጫካ ምንጣሮ ስራ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ኮርፖሬሽን ስራውን በመውሰድና 2 ቢሊየን 92 ሚሊየን 303 ሺህ 113 ብር ከ22 ሳንቲም በመቀበል፥ ስራውን በሌሎች ንዑስ ተቋራጮች ያለ ምንም ጨረታ በመስጠት የምንጣሮ ስራው በአግባቡ ተመንጥሮ ሳያልቅ ገንዘብ ወጪ በማድረግ ክፍያ በመፈፀምና ቀሪ ገንዘብ የት እንዳለ ባለመታወቁ ለግል ጥቅምና ሌሎች እንዲጠቀሙ በማድረግ ከዚህ ባለፈም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ኮርፖሬሽን ኮርፖሬሽኑ ከተቋቋመበት አላማ ውጭ እንዲሁም ከፋይናንስ ህግ ውጭ በሆነ ሁኔታ በነሃሴ ወር 2003 ዓ.ም ለአቤራ ኪነ ጥበባት ማዕከል ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በስፖንሰር መልክ 536 ሺህ ብር በመስጠትና 306 ሺህ ብር በብድር መልክ መስጠትና የተበደረው ተቋም ገንዘብ ያልተከፈለ መሆኑ፥ የኮርፖሬሽኑ አባላት ያልሆኑትን አባላት እንደሆኑ በደብዳቤ በመግለጽ ለተጠርጣሪ #ፍጹም_የሽጥላ_በቀለ እና ለአቶ #ተስፋሁን_ሰብስቤ ለ30 ቀን የአሜሪካ ቆይታ 23 ሺህ ዶላር በሃምሌ ወር 2008 ዓ.ም እንዲከፈል በማድረግ፤ እንዲሁም ለአቶ #ዝናህብዙ_ፀጋዬ ለ20 ቀን የአሜሪካ ጉዞና ቆይታ 7 ሺህ 687 ከ50 ዶላር ከንግድ ባንክ እንዲከፈል በማድረግ ወጪው ከኮርፖሬት ፋይናንስ ኢንቨስትመንት እንዲሸፈን ደብዳቤ በመጻፍ፣ ለኮሎኔል አታክልት ወልደሚካኤል #ልጅ ዮናስ አታክልት የውጭ ሃገር ህክምና 86 ሺህ 889 ሺህ ከ54 ዶላር ክፍያ እንዲፈጸም በማድረግ፣ ለወይዘሮ ንግስቲ ከሰተ የውጭ ሃገር ህክምና 18 ሺህ 454 ሺህ 51 ዶላር ክፍያ እንዲፈጸምና ሌሎችም እንዲጠቀሙ ክፍያ እንዲፈጸም በማድረግ በ2004 ዓ.ም የግዥ ዘመን ከግዥ መመሪያ ውጭ አለም አቀፍ የጨረታ ውድድር ሳይደረግ ከመስሪያ ቤቱ ሃላፊዎቹ ጋር በመሆን የግዥ ውል በማፅደቅ 10 ሚሊየን 670 ሺህ 184 ዶላር በማውጣት፥ ኖሮኮን ከተባለው የቻይና ኩባንያ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች ግዥ በህገ ወጥ መንገድ እንዲፈጸም በማድረግ መንግስት ከጨረታ ውድድር ሊያገኝ የሚገባውን ጥቅም በማሳጣት ከግዥ መመሪያ ውጭ አለም አቀፍ ጨረታ ውድድር ሳይደረግ ከመስሪያ ቤቱ ሃላፊዎች ጋር በመሆን የግዥ ውል በማፅደቅ 660 ሺህ ዶላር በማውጣት፥ ዳኑቢያን ኤርክራፍት ከተባለ አለም አቀፍ ድርጅት የአገልግሎት ግዥ በህገ ወጥ መንገድ እንዲፈጸም በማድረግ መንግስት ከጨረታ ውድድር ሊያገኝ የሚገባውን ጥቅም በማሳጣት፤ ሜቴክ ከ2001 ዓ.ም ጀምሮ ከ13 በላይ አለም አቀፍ ኩባንያዎችን ያለምንም ጨረታ እና ውድድር በሰላሳ የተለያዩ የውል ስምምነቶች ከአንድ ቢሊየን ዶላር በላይ የሚያወጡ ግዥዎች እንዲከወኑ ተደርጓል፤ ተጠርጣሪው እነዚህ ውሎች ውስጥ ለጊዜው የተረጋገጠ 15 የሚሆኑ ውሎችን አፅድቀዋል እንዲሁም ተፈራርመዋል።

የእርሳቸው #ወንድም የሆኑት አቶ ኢሳያስ ዳኘውን የተጠረጠሩባቸውን የሙስና ወንጀሎችም ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል። በዚህም ግለሰቡ የኢትዮ ቴሌኮም የኤን ጂ ፒ ኦ ፕሮግራም ዳይሬክተር ሆነው ሲሰሩ ለሜቴክ በሶማሌ ክልልና በባሌ ዞን የሞባይልና ሲ ዲ ኤም ኤ ሳይቶች ግንባታ ስራ፥ 204 ሚሊየን 981 ሺህ 630 ብር የተደረገው ውል ስራው ሳይጠናቀቅ ቫትን ጨምሮ 322 ሚሊየን 628 ሺህ 124 ብር ከ55 ሳንቲም ክፍያ እንዲፈጸም ለፋይናንስ ደብዳቤ በመጻፍ ደረጃውን ያልጠበቀና ጥራት የሌለው ስራ እንዲሰራ በማድረግ፣ እንዲሁም ስራው ሳይጠናቀቅ የመጀመሪያውን ውል በማሻሻል የቴሌ ታወር ግንባታና ተከላ ስራ 321 ሚሊየን 710 ሺህ 424 ብር ከ55 ሳንቲም ውል በማሻሻል ለሜቴክ በመስጠት የተጠረጠሩ ናቸው ብሏል።

ከዚህ ባለፈም በአቶ #ተስፋዬ_ኡርጌ_ላያ ባደረገው ምርመራ ተጠርጣሪው ፈጽመዋቸዋል ያላቸውን ድርጊቶች በጽሁፍ አቅርቧል፤ በዚህም ግለሰቡ የተለያ ሰዎችን የኦነግ ድርጅት አባል ናቸሁ በማለትና ያለአግባብ እንዲታሰሩ በማድረግ በስውር እስር ቤት በማሰርና በማሰቃየት እንዲሁም በማስፈራራት ከሌሎች ግብረ አበሮቻቸው ጋር 6 ሚሊየን ብር እና 22 ሺህ ዶላር በመቀበል ለግል ጥቅማቸው አውለዋል ሲል ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።

የደረሰውን ጉዳት ኦዲት ማስደረግ፣ ያለጥቅም የተቀመጠውን ፋብሪካ ያለበትን ደረጃ የባለሙያ ቃል መቀበልና የምስክሮች ቃልን መቀበልን ጨምሮ ሌሎች ቀሪ ስራዎች እንዳሉትም ለችሎቱ አስረድቷል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikahethiopia
#update ሜጀር ጀነራል #ክንፈ_ዳኘውን ጨምሮ 8 ተከሳሾች ክሳቸው እንዲሻሻል ፍ/ቤት ትዕዛዝ ሰጠ። እነ ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ትራክተሮችን ያለጨረታና የግዥ መመሪያ ከሚፈቅደው ሥርዓት ውጭ የጥራት ችግር ያለባቸው ዕቃዎችን በመግዛት 119,856,756.23 ብር በህዝብና በመንግስት ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ተከሰው ፍርድ ቤት መቅረባቸው ይታወሳል፡፡ ተከሳሾቹ የካቲት 26 ቀን 2011 ዓ.ም. በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 15ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡ ሲሆን ከዚህ ቀደም ይዘውት በቀረቡት የክስ መቃወሚያ ላይ የተወሰኑ ክሶች እንዲሻሻሉ ፍ/ቤቱ ብይን ሰጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት በቀረበው የክስ መቃወሚያ ላይ ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘውን ጨምሮ 8 ተከሳሾች ከትራክተር ግዥ ጋር በተያያዘ ክሱ እንዲሻሻል ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ በተሸሻለው ክስ ላይ ክርክር ለማድረግ እና ተገቢውን ትዕዛዝ ለመስጠት ፍርድ ቤቱ ለመጋቢት 5/2011 ዓ.ም. ተለዋጭ የጊዜ ቀጠሮ መስጠቱን ከጠቅላይ አቃቤ ሕግ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia