TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የምስራች🎊 ከረድኤት አስመጪ ቅናሽ አድርጓል!!

Konica minolta 451/550/650 በ 70 ሺብር ብቻ የምናቀርባቸውን ምርቶች ሲገዙ በተመጣጣ ዋጋ ከሙሉ የጥገና ዋስትና ጋር እናስረክባለን!!

ይምጡና ይጎብኙን አድራሻችን፦ አዲስ አበባ ሜክሲኮ #ኬኬር_ህንፃ ግራውንድ ስር እንገኛለን

ስልክ፦
+251904141404
+251902477474
#update ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከሶማሊያና ከቦስትዋና ፕሬዝዳንቶች ጋር ውይይት አደረጉ። እየተካሔደ በሚገኘው 32ተኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሞሃመድ አብዱላሂ ፋርማጆ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።
በተመሳሳይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከቦስትዋና ፕሬዝዳንት ጋር ውይይት እያደረጉ ናቸው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለሰራተኞቹ ሽልማት ተበረከተ‼️

የገቢዎች ሚኒስትር ወይዘሮ አዳነች አበቤ የቶጎ ጫሌና ጅግጅጋ ጉምሩክ ኮሚሽን ቅርንጫፍ ሰራተኞች የኮንትሮባንድ ንግድን በመቆጣጠር ላበረከቱት አስተዋፅኦ የተለያዩ ሽልማቶችን አበርክተዋለ ።

ሚኒስትሯ በትናንትናው ዕለት በጂጂጋና ቶጎ ጫሌጉምሩክ ኮሚሽን ቅርንጫፍ ለራሳቸው ጥቅም ሳይታለሉ ህገ ወጥ ንግድን በተገቢ ሁኔታ ለተፋለሙ በሁሉም የስራ መደብ ለሚገኙ ሰራተኞች የማበረታተች ሽልመት ሰጥተዋል ።

ሽልማቶችም ዘመናዊ ሳምሰንግ ሞባይል S9 (+) ቀፎዎች ፣ ዘመናዊ ላፐ ቶፕ፣ አንድ ኤፍ.ኤስ.አ እና ፒክ አፕ መኪናዎች መሆናቸውን ከገቢዎች ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ወይዘሮ አዳነች በሽልማት ስነ ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር ህገ ወጥ ንግድን መከላከልና መቆጣጠር ሀገርና ሕዝብን ከውድቀት ማዳን መሆኑን ተናግረዋል።

ሽልማቱ ሰራተኞች በስራቸው ላስመዘገቡት ስኬት የተበረከተ መሆኑን በመጥቀስ ለሀገርና ለወገን በጥቅማ ጥቅም ሳይንበረከክ ለሚሰራ ሽልማት ይገበዋል ብለዋል።

ከዚህ ባለፈም ሀገራችን ካለችበት ዘርፈ ብዙ ችግር ውስት ለማውጣት ከዚህ በተሻለ በጋራ እና በቅንጅት ልንሰራ ይገባል ነው ያሉት።

በኮንትሮባንድ የሚገቡ የጦር መሳሪያዎች፣ ጊዜያቸዉ ያለፈባቸው መድሃኒቶችና መሰል ሸቀጦች ዜጎችን ለዘርፍ ብዙ ችግሮች ከመዳረጋቸው በሻገር የሀገርና የህዝብን ራዕይ የሚያጨልሙ መሆናቸውን አንስተዋል።

ስለሆነም የኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል የጉምሩክ ሰራተኞችና አጠቃላ ህብረተሰቡና የፀጥታ አካላት ከክልሉ መንግስት ጋር በቅንጅት እየሰሩት ያለዉ ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

ሽልማቱን ባልጠበቁት ሰዓት ከሚንስትሯ እጅ የተቀበሉ ሰራተኞች በበኩላቸው ሽልማቱ የተሰጠንን ሀላፊነት በተገቢው ሁኔታ እየሰራን ነው የሚል ስሜት እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል።

በቀጣይም የኮንትሮባንድን ንግድ አመርቂ በመሆነ መልኩ ለመቆጣጠር የበኩላቸውን አስተወፅኦ የሚያበረክቱ መሆኑን ነው የገለፁት።

በቶጎ ጫሌና ጅግጅጋ ጉምሩክ ኮሚሽን ቅርንጫፍ በተለያየ ጊዜ በርካታ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በሰራተኞች ክትትል በቁጥጥር ስር ማዋላቸው ይታወሳል።

በቅርቡም በቶጎ ጫሌ ጉምሩክ ኮሚሽን ቅርንጫፍ 7 ኪሎ ግራም ወርቅን ጨምሮ 60 ሚሊየን የሚገመቱ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወቃል።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Fake News Alert‼️

(ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)

በርካታ ጋዜጠኞች፣ አክቲቪስቶች እና ብዙ የሶሻል ሚድያ ተከታታይ ያላቸው ግለሰቦች የአፍሪካ ህብረት አማርኛን ስድስተኛ የስራ ቋንቋው አድርጎ እንደመረጠ ትናንት ሲፅፉ ነበር። እውን ሆኖ "እልል" ባስባሉን እያልኩ ነበር፣ ነገር ግን መረጃው #የሀሰት ነው።

ዛሬ በጠዋቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ቃል አቀባይ የሆነችው ኤባ ካሎንዶ ጋር ደወልኩ። በመልሷም፦

"የቋንቋ ምርጫ የመሪዎቹ አጀንዳ ላይ ጭራሽ አልነበረም። እርግጥ ጠ/ሚር አብይ ስለ አፍሪካ ሀገር በቀል ቋንቋዎች ጥቅም አውርተዋል። የኢኳቶርያል ጊኒው መሪም ቋንቋቸው የአፍሪካ ህብረት ቋንቋ እንዲሆን ይፈልጋሉ። ይህ ማለት ግን ሆኑ ማለት አይደለም። ስለዚህ ኤልያስ፣ አማርኛ የአፍሪካ ህብረት ኦፊሴላዊ ቋንቋ ሆነ የተባለው የሀሰት ዜና (fake news) ነው።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አማርኛ‼️
.
.
#የቋንቋ_ምርጫ የመሪዎቹ አጀንዳ ላይ #ጭራሽ_አልነበረም ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋቂ ተናገሩ። ሊቀመንበሩ ለAPው ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት እንደተናገሩት ጠ/ሚር አብይ ስለ አፍሪካ ሀገር በቀል ቋንቋዎች ጥቅም አውርተዋል፤ የኢኳቶርያል ጊኒው መሪም ቋንቋቸው የአፍሪካ ህብረት ቋንቋ እንዲሆን ይፈልጋሉ፤ ይህ ማለት ግን ሆኑ ማለት አይደለም ብለዋል። ትላንት ምሽት በማህበራዊ ሚዲያ አማርኛ የአፍሪካ ህብረት ኦፊሴላዊ ቋንቋ ሆነ የተባለውም የሀሰት ዜና (fake news) ሲሉ ተናግረዋል።

#TIKVAHETHIOPIA #ቲክቫህኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Fake News Alert‼️

"ከላይ የምታዩት ደብዳቤ ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ለሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንደተላከ ተደርጎ የተሰራ ሃሰተኛና ከሃቅ የራቀ ደብዳቤ መሆኑን እንገልጻለን፡፡"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀሰተኛ መረጃ‼️

ለውድ መምህራን በሙሉ፦

ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን ደመወዝ #የተጨመረ በማስመሰል #የተሣሣተ_መረጃ እየተሠራጨ ይገኛል። ስለዚህ መረጃው ከእውነት የራቀና ሀሠት መሆኑን የሣይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን የገለፀልን መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን።

የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወለጋ ዩኒቨርሲቲ‼️

የወለጋ ዩኒቨርሲቲ በፀጥታ ችግር #የባከነውን የትምህርት ጊዜ #ለማካካስ የእረፍት ቀናት ጨምሮ እየሰራ መሆኑን ገለጸ፡፡

በጸጥታ ችግር ምክንያት የባከነ የትምህርት ጊዜን በማካካስ የመጀመሪያውን መንፈቅ ዓመት በስኬት ለማጠናቀቅ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆናቸውን የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና መምህራን ለኢዜአ ገልጸዋል።

አሁን አንጻራዊ #ሰላም በመስፈኑ ተቋሙ ያመቻቸላቸውን የትምህርት ማራዘሚያ ጊዜ በመጠቀም የባከነውን ጊዜ ለማካካስ ከመምህራን ጋር እየሰሩ እንደሚገኙ ተማሪዎች ገልጸዋል።

የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ዘላለም አብዲሳ በበኩላቸው በምዕራቡ ክፍል ተፈጥሮ በነበረው የጸጥታ ችግር ለተወሰነ ጊዜ የባከነውን የትምህርት ጊዜ ለማካካስ የሁለት ሳምንት ማራዘሚያ ተደርጓል።
በእረፍት ቀናትም ጭምር የማካካሻ ትምህርቱ እየተሰጠ መሆኑን ገልፀዋል።

በተለይ ለሴት ተማሪዎች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት መዘጋጀቱን የገለፁት ምክትል ፕሬዚዳንቱ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ስራን ለማስቀጠል እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በ1999 ዓ.ም 851 ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር የጀመረው የወለጋ ዩኒቨርሲቲ በአሁኑ ወቅት በመደበኛና ተከታታይ የትምህርት መርሀ ግብር በመጀመሪያ፣ በሁለተኛና በሦስተኛ ዲግሪ 38 ሺህ ተማሪዎች በማስተማር ላይ መሆኑ ታውቋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የቦሌ ክፍለ ከተማ ስራ አስኪያጅ #ጥላሁን_ፍቃዱ በክፍለ ከተማው ወረዳ አንድ የነዋሪነት መታወቂያ ያላግባብ ተሰጥቷል መባሉን አስተባብለዋል፡፡ ሸገር ራዲዮ ቀደም ሲል ወረዳው ለ2 ሺህ ዜጎች ያላግባብ መታወቂያ መሰጠቱን ጠቅሶ ያሰራጨውን ዘገባ መሠረት በማድረግ ማጣራት ተደርጓል ብለዋል፡፡ ሆኖም ለጊዜያዊ ሥራ ፈጠራ ዕድል ሲባል በቀጠናው ነዋሪነታቸው ለተረጋገጠላቸው 597 ወጣቶች መታወቂያ ከመሰጠቱ በስተቀር ሌላ የተሰጠ መታወቂያ የለም፡፡ አንድ የወረዳው ሠራተኛ መረጃውን ለሸገር በማድረሳቸው ብቻ ከሥራ ስለመታገዳቸው መረጃ የለኝም ብለዋል፡፡

via wazemaradio
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ከአልጄሪያ፣ ከሞሮኮ፣ ከቱኒሲያና ከኤስቶንያ መሪዎች ጋር በጋራ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።

ምንጭ፤ ጠ/ሚኒስትር ጽ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጋዜጠኛ ዳዊት እንደሻው...

"ደቡብ ጎንደር ዞን ምስራቅ #እስቴ_ወረዳ እሁድ የካቲት 3 ከለሊቱ 10 ሰዓት ላይ አንድ መስጅድ በግለሰቦች ተቃጥሎ ማደሩን ከአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ሼክ ሙሐመድ ሐሰን አረጋግጫለሁ፡፡"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ደቡብ ጎንደር‼️

በደቡብ ጎንደር ዞን ትናንት ምሽት አንድ #መስጂድ ላይ #የእሳት_አደጋ ደረሰ። በደቡብ ጎንደር ዞን አንዳቤት ወረዳ ጃራ ገዶ አካባቢ አደጋው የደረሰው ትላንት ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ ነው፡፡

የአማራ ክልል መንግስት ኮሙኒኬሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ #መላኩ_አላምረው እንደተናገሩት የቃጠሎ አደጋው በጨለማ መፈፀሙ ከድርጊቱ ጀርባ #የተደራጀ ቡድን መኖሩን ያመላክታል፡፡ ይህም የዳር አገሩን ግጭት ወደ መሃል አገር ለማምጣት ሙከራ እየተደረገ መሆኑን ክልሉ መገንዘቡን አቶ መላኩ ተናግረዋል፡፡

ክልሉ የአደጋውን ሁኔታ የሚከታተል #አጣሪ ቡድን ወደ ስፍራው መላኩንም አመልክቷል፡፡ ቃጠሎ የደረሰበትን መስጂድ ለማጥፋት የአካባቢው ህብረተሰብ ርብርብ ማድረጉንና መስጅዱን መልሶ ለመገንባት ገንዘብ በማሰባሰብ ላይ መሆኑም ተመልክቷል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በደቡብ ጎንደር እስቴ ላይ በሁለት መስጅዶች ቃጠሎ ጋር በተያያዘ እጃቸው አለበት የተባሉ 6 ተጠርጣሪዎችን የክልሉ ፖሊስ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ መላኩ ገልጸዋል፡፡

ከመስጊድ ቃጠሎው ጀርባ በአካባቢው #የሚንቀሳቅስ ህቡዕ ቡድን መኖሩ እንደተደረሰበትና ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ክልሉ እየሰራ መሆኑን ምክትል ኃላፊው አስረድተዋል፡፡

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በደቡብ ጎንደር ተጨማሪ መስጊድ ተቃጠለ‼️

በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን በጃራ ገዱ አነስተኛ ከተማ ያለ መስጊድ ባልታወቁ ሰዎች ትላንት ለሊት መቃጠሉን የአካባቢው የእስልምና ጉዳይ ምክር ቤት እና የዞኑ አስተዳደር አስታወቁ። ቃጠሎው #ሆን_ተብሎ ለመደረጉ ጠቋሚ ምልክቶች መገኘታቸውንም ገልጿል።

ቃጠሎው የደረሰበት የጃራ ገዱ ከደቡብ ጎንደር ዞን ዋና ከተማ ደብረ ታቦር 100 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ከተማዋ የምትገኝበት የአንዳ ቤት ወረዳ የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት (መጅሊስ) ዋና ጸሐፊ አቶ #እንድሪስ_ሱፊያን ለጀርመን ራድዮ እንደተናገሩት የትላንቱ ቃጠሎ የደረሰው ከለሊቱ ሰባት ሰዓት ገደማ ነው። በቃጠሎውም “ለአካባቢው ብቸኛ የሆነው መስጊድ ወድሟል” ብለዋል።

“ለሊት ላይ #የተኩስ ድምፅ ሰምተን ወደ ቦታው ሔድን፤ ማትረፍ አልተቻለም። ሁሉም ተያይዞ ነው ያገኘንው። በራፉን ሰብረው ገብተው ነው። ቁልፉ ራሱ የተቆለፈበት አልወጣም። እንዳለ ነው የተዘጋበትን ነቅለው ከውስጥ ያሉ አንዳንድ ቁሳቁሶችን አውጥተው አቃጥለውት ያገኘንው። አብዛኞቻችን ጣራው እና ግድግዳው በእሳት ተበልቶ ነው የደረስንው” ሲሉ ዋና ጸሐፊው የዓይን እማኝነታቸውን ሰጥተዋል።

አደጋው መድረሱን ያረጋገጠው የደቡብ ጎንደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት በበኩሉ መስጊዱ የተቃጠለው “በሩ ተሰብሮ ተከፍቶ ከውስጥ ያሉ መፅሀፍት ሲቃጠሉ ተያይዞ መስጊዱ በመቀጣጠሉ” መሆኑን በፌስ ቡክ ገጹ አስታውቋል። ድርጊቱን የፈጸመው አካል ማንነትን ለማጋለጥ ከአካባቢው ነዋሪ ጋር ዛሬ ስብሰባ መካሄዱንም ገልጿል። እስከ እኩለ ቀን በዘለቀው በዚሁ ስብሰባ የዞን እና የወረዳ ኃላፊዎች ተገኝተዋል ተብሏል።

መስጊዱን በማቃጠል የተጠረጠሩ ግለሰቦች እስካሁን አለመያዛቸውን የሚናገሩት የአካባቢው የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ድርጊቱ “ሆን ተብሎ የተፈጸመ ለመሆኑ አመላካች ናቸው” ያሏቸውን ለጀርመን ድምፅ ራድዮ ዘርዝረዋል። “ከፍርስራሹ ማየት እንደቻልነው መስጊድ ውስጥ ሆን ተብሎ ቁርአኖች ተሰብስበው አንድ ቦታ ነው የተቃጠሉት። ሁለተኛ ደግሞ ቁርአኖች የሚደረደሩበት መደርደሪያዎች ከቃጠሎው የተረፈው ነገር አልተገኘም፤ እንዳለ መውጣቱን ያመለክታል። ሌላኛው ደግሞ የመስጊዱ ምንጣፎች ሌላ ሰዋራ፣ ዘወር ያለ ቦታ ቁጥቋጦ ስር ደብቀውት ከረፈደ በኋላ እርሱንም ለማግኘት ተችሏል” ሲሉ አቶ እንድሪስ አስረድተዋል።

በደቡብ ጎንደር ዞን መስጊድ ሲቃጠል በአንድ ሳምንት ውስጥ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ ነው። የትላንትናው ቃጠሎ የደረሰበት የጃራ ገዶ ቀበሌ ሁለት መስጊዶች ከተቃጠሉበት የእስቴ ወረዳ በ50 ኪሎ ሜትር ገደማ ርቀት ላይ የሚገኝ ነው። በጃራ ገዱ ጊዜያዊ የመስገጃ ቦታ ለመቀለስ እና የተቃጠለውን መስጊድ መልሶ ለመገንባት የአካባቢው ነዋሪዎች በምክክር ላይ መሆናቸውን የአካባቢው የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ለጀርመን ራድዮ ተናግረዋል።

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
6 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ‼️

በደቡብ ጎንደር #እስቴ_ወረዳ ላይ ከሁለት መስጅዶች ቃጠሎ ጋር በተያያዘ #እጃቸው አለበት የተባሉ 6 #ተጠርጣሪዎች በአማራ ክልል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#update በደቡብ ጎንደር ዞን በመስጊዶች ላይ የደረሰውን ቃጠሎ በፅኑ #እንደሚያወግዝ የኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ አስታወቀ፡፡
በተመሳሳይ በደቡብ ክልል ሀላባ ዞን የደረሰውን የቤተ እምነቶች ቃጠሎም #አውግዟል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#update በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን በሚገኙ ሁለት ወረዳዎች በመስጊዶች ላይ የደረሱ ጥቃቶችን አጥብቆ #እንደሚያወግዝ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ገለፀ፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ተጠርጣሪዎቹ ከእስር እየተለቀቁ ነው‼️

የድሬደዋ አስተዳደር በቅርቡ በከተማው በተካሄደው ተቃውሞ እና ሁከት ጋር በተያያዘ #ጠረጠርኳቸው በሚል በቁጥጥር ስር ካዋላቸው ከሦስት መቶ በላይ ሰዎች የአብዛኞቹን ክስ በማቋረጥ በነፃ እየለቀቀ ይገኛል። ከቀናት አስር በኃላ በቂ ማስረጃ ባለመኖሩ የተለቀቁ ተጠርጣሪዎችና ቤተሰቦች እንዲሁም ወዳጆች በእምባ ተራጭተዋል፡፡ በከተማው ለቀናት የተከሰተውን ተቃውሞ ተከትሎ የፀጥታ ሀይሉ በወሰደው ሰፊ እርምጃ ከሶስት መቶ በላይ የሚሆኑ ተጠርጣሪዎችን አፍሶ በመያዝ ከአስራ አምስት ቀናት በላይ በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው ሲመረመር ቆይቷል፡፡ ከነዚህ ተጠርጣሪዎች ሁለት መቶ አስራ ስምንት የሚሆኑትን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ እና ፖሊስ ውሰኔ ክሳቸው ተቋርጦ በነፃ እንዲለቀቁ ተደርጓል፡፡

ከሳምንት በፊት በሀላፊነት የተሾሙት የአስተዳደር ፖሊስ ኮምሽን ኮምሽነር ኮማንደር አለሙ መርጋ ተጠርጣሪዎቹ ስለተለቀቁበት ምክንያት አስረድተዋል፡፡

ከትናንት በስቲያ ጀምሮ ተጠርጣሪዎችን በመልቀቅ ላይ የሚገኙት ጠቅላይ ዐቃቤ ህግና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ከመልቀቃቸው በፊት ከተጠርጣሪዎች ፣ ከቤተሰብና በነፃ ጥብቅና ቆመው ከነበሩ የህግ ባለሞያዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል። ኮምሽነሩ ስለውይይቱ ዓላማ ተናግረዋል፡፡ በተለያዩ ቀናት በተካሄደው በዚህ ውይይት በከተማው የተፈጠረውን ሁከት ተከትሎ በጅምላ ተይዘው የቆዩ ተጠርጣሪዎች ከድርጊቱ ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት ሳይኖር ጭምር መሆኑነንና፣ በምርመራ ሂደትም ከመርማሪዎች ከብቃት ጋር የተያያዙ ችግሮች እንደነበሩ ተነስተዋል፡፡ ወጣቶቹም #በሰላማዊ መንገድ ትግላችንን እንቐጥላለል ብለዋል፡፡

ከህብረተሰቡ ለተነሱት ጉዳዮች በፖሊስ እና ዐቃቤ ህግ በኩል ተወስደው የሚታረሙ መሆኑ ተገልፇል፡፡ በሌላ በኩል ከዚሁ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው ፍ/ቤት ቀርበው ግዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸው ከነበሩና ዛሬ ፍርድ ቤት ከሚቀርቡ ዘጠና ተጠርጣሪዎች አብዛኞቹን ክስ በማቋረጥ መልቀቃቸው ለፍ/ቤቱ ተገልፃል፡፡

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia