TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊያዳምጠው የሚገባ🔝

ሳምቡሳ ጠባሹ ሶርያዊ ስደተኛ በኢትዮጵያ፣ በሸገር ከልዩ ወሬፕሮግራም ቀርቦ እንዲህ አለ::

“የእኔ ሐገር ሶርያስ #ፈርሳለች#ቆንጆ ሐገር አላችሁ፤ ሐገራችሁን ጠብቋት”…ሶርያዊውን ሙዙሪ ጉድሃን አል ሙድሉሽ ከሐገሩ ያስወጣው አሰቃቂው የሶርያ ጦርነት ነው ኢትዮጵያ ያመጣው ደግሞ ፍቅር !

አዎ ፍቅር ! የሶርያን መፍረስ ተከትሎ ሐገር ለሐገር ሲዞር ሊባኖስ ደረሰ፡፡ እዛም ከአንዲት ኢትዮጵያዊት ሴት ጋር ተዋድዶ ኢትዮጵያ ይዛው መጣች፡፡ “ምርጥ ሐገር…” ይላል፣ “በተለይ አየራችሁ ሲያምር…”

አዲሱ ገበያ ታክሲ ተራው ጋር መሸትሸት ሲል ሳምቡሳ ይጠብሳል፤ የሐገሩን ጣፋጮችም ይሸጣል፡፡ ከኢትዮጵያዊት ሚስቱ አንድ ልጅ ወልዶ አብረው እየኖሩ ነው፡፡ ሳምቡሳ እየጠበሰ፣ ጣፋጭ እየሸጠ ሚስቱን እና ልጁን ያስተዳድራል፡፡ አማርኛ ጥሩ ይናገራል፡፡ በ3 ወር ነወ የለመድኩት ይላል፡፡ ማንበብም ይችላል፡፡ መፃፍ እየሞከርኩ ነው ይላል፡፡ ሐማ የምትሰኘው የሶርያ ከተማ ውስጥ ነበር የሚኖረው፡፡ በአረብኛ ሥነፅሁፍ የመጀመሪያ ዲግሪ አለው፡፡ ምን ዋጋ አለው - የሶርያ ጦርነት ሲቀሰቀስ ሁሉም ነገር በንኖ ጠፋ፡፡

በጦርነቱ አንድም ዘመድ አልተረፈውም፡፡ በዚህች ምድር ያሉኝ ዘመዶቼ ኢትዮጵያዊቷ ባለቤቴ እና ልጄ ናቸው ይላል፡፡ የበርካታ ሙያዎች ባለቤት የሆነው ሶርያዊው ሙዙሪ ጉድሃን አል ሙድሉሽ፣ ከ250 በላይ ምግቦች መስራት እችላለሁም ነው የሚለው… ከምንም በላይ ግን ለኢዮጵያውያን የሚያስተላልፈው መልእክቱ ይህ ነው - “ሰላም ከሌለ ምንም ነገር የለም…”

ምንጭ:-ሸገር FM
@tsegabwolde @tikvahethiopia