TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ፍትህ ለእህቶቻችን⬆️

ከሳምንት በፊት በአዲስ አበባ ከተማ #ቡልጋሪያ አካባቢ ስለደረሰ የመኪና አደጋ መረጃ ሰጥቻችሁ ነበር። አደጋው በሁለት ሴቶች ላይ የደረሰና አደጋውን ያደረሰው የፖሊስ መኪና እንደነበር አይዘነጋም። በነገራችን ላይ አደጋው የደረሰባቸው እህትማማቾች ነበሩ። በዚህ አደጋ የወጣት #ሳራ_ተወልደ ህይወት ወዲያው ሲያልፍ እህቷ #እየሩስ በወቅቱ ለህክምና እርዳታ ሆስፒታል ብትገባም ህይወቷን ማትረፍ አልተቻለም። እንግዴ ከአንድ ቤት ሁለት ሰው ማጣት ቤተሰቡን ምንኛ በሀዘን እንደሚጎዳ መገመት ቀላል ነው።

ዛሬ ደግሞ የሰማሁት እጅግ በጣም አሳዛኝ መረጃ ነው። የመኪና አደጋውን ያደረሰው ግለሰብ እስከዛሬ ለፍርድ አልቀረበም፤ በህግም አልተጠየቀም። ቤተሰቦች #ፍትህ እየጠየቁ ናቸው። አደጋውን ያደረሰው ግለሰብ ለፍርድ እንዲቀርብ እና እንዲጠየቅም ቤተሰቦች ጠይቀዋል።

የሚመለከተው አካል ይህን ጉዳይ ተከታትሎ አጥፊውን ለፍርድ ሊያቀርብ ይገባል‼️

የህግ የበላይነት ይረጋገጥ!
ፍትህ ለእህቶቻችን!
@tsegabwolde @tikvahethiopia