TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ዘንድሮም በነፃ⬆️አልበርት የማጠናከሪያና የበጎ አድራጎት ማዕከል። #አዳማ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኦሮሚያ ክልል⬇️

በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች የሕግ የበላይነትን ለማስከበርና ሕገ ወጥነትን ለመከላከል በተሰራው ስራ የተለያዩ ሕጋዊ እርምጃዎች ተወስደዋል፡፡

#ሱሉልታ

በቄሮ ስም እንቅስቃሴ በማድረግ ሌሊት የግለሰቦችን ቤት በማፍረስና ቆርቆሮ በመውሰድ ላይ የተሰማሩ 4 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር
ውለዋል፡፡

#ሻሸመኔ

ባለፈው ሳምንት በከተማው የተፈጸመው ወንጀል እጃቸው አለበት ተብለው የተጠረጠሩ 7 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

#ቡራዩ

የቄሮ አመራር ነኝ በማለት መታወቂያ አዘጋጅቶ የተለያዩ ተቋማት በግድ ስፖንሰር እንዲያደርጉት ሲጠይቅ የነበረ፣ ቲተር: ማዕተምና የመታወቂያ ወረቀት በቄሮ ስም አዘጋጅቶ በመሸጥ ሲነግድ የነበረ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

#ለገጣፎ_ለገዳዲ

በቄሮ ስም የ62 ወጣቶችን ፎቶ በማሰባሰብና ወረቀት ላይ በመለጠፍ የቄሮ አደረጃጀት ከቀበሌ እስከ ላይ መኖር አለበት በሚል ወጣቶችን
ሲያታልሉና ሲያደረጁ የነበሩ 2 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

#ጅማ

በሕገ ወጥ ስራ ላይ ተሰማርተው ሕገ ወጥ ግንባታ ሲያካሄዱ የነበሩ 42 ሰዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 8 ሰዎች ላይ ሙሉ መረጃ ተሰባስቦ ለሕግ ሊቀርቡ ነው፡፡
ድንገት በተደረገው ፍተሻም 2ሽጉጥና 180 ጥይቶች ተይዘዋል፡፡

#አዳማ

በቅርቡ በከተማው ለተከሰተው ግጭት መነሻ በመሆን ሰዎችን ሲያነሳሱ የነበሩና ግጭቱ የብሔር መልክ እንዲይዝ አድርገዋል የተባሉ 8 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

#ሞጆ

ጨለማን ተገን በማድረግ ፋብሪካን ለመዝረፍ ሲንቀሳቁ የነበሩ 2 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፣ በአንደኛው ግለሰብ እጅ ሽጉጥ ተይዟል፡፡

#ሰበታ

በሕገ ወጥ ግንባታ ላይ የተሰማሩ፣ ምግብ ቤት ገብተው በመመገብ ሒሳብ የማይከፍሉና ተደራጅተው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 14 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

ምንጭ:- የኦሮሚያ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
እንኳን ተረፋቹልን...

"ዛሬ 10 ሰዓት አካባቢ #ከሃዋሳ ወደ #አዳማ ይዞን ይጓዝ የነበረ FSR ቅጥቅጥ ባስ ተገልብጦብን 1 ሰው ከባድ ጉዳት ደርሶበታል፤ ሌሎቻችን ምንም አልሆንም"

@tsegabwolde @tikvahethipia
ነገ አበበች ጎበና ምን ይዤ ልምጣ?

ፍቅርን፣ አንድነትን፣ መዋደድን፣ ሰውን በሰውነቱ ማክበርን፣ የሀገር ፍቅርን፣ መከባበርን፣ መቻቻልን ከንፁህ ልባችሁ ጋር ይዛችሁ ኑ!!

እንደው እንደው የምትሆኑበት ቦታ የሚያመቻችሁ ከሆነና የትችሉ ከሆነ ደግሞ፦

በህፃናት እንክብካቤና የልማት ድርጅቱ ከ1ኛ ክፍል እስከ 8ኛ ክፍል ድረስ በእናታችን አበበች ጎበና ስር ያሉ ልጆሽ አሉ በመሆኑም ቤት ውስጥ ትንንሽ መጠን ያላቸው ልብሶች፣ እስክርቢቶ/አንድም ቢሆን/፣ የልጆች መፅሃፍ፣ ደብተር/አንድ ነጠላም ቢሆን/ ይዛችሁ መምጣት ትችላላችሁ።

ኑ ከእናታችን ምርቃት እንቀበል!!

ቀጠሮ ይከበር ~ 6:00 ሰዓት

ቦታው፦

R= ቅዱስ ዮሐንስ ወልደነጎድጓድ ቤተክርስቲያን (ከፒያሳ ታክሲ መያዝ ይቻላል)

T1= ከዮሐንስ ቤተክርስቲያን ወደ ጎጃም በረንዳ በሚወስደው መንገድ ሲመጡ የኢትዮጲያ ንግድ ባንክ ጎጃም በረንዳ ቅርንጫፍን ያገኛሉ፡፡ አስፓልቱን ትተው ቀጥታ የሚወስደውን ኮብልስቶን መንገድ ይዘው ይጓዙ

T2= ኮብልስቶኑን ተከትለው ቀጥታ ሲጓዙ የአስፓልት መንገድ ያገኛሉ ከዛም ወደ ቀኝ(ወደ ላይ) ይታጠፋሉ፡፡

T3= አስፓልቱን እንደያዙ ወደ ላይ ትንሽ ከፍ እንዳሉ ወደ ድርጅቱ መግቢያ ያገኛሉ፡፡

📌 በተጠቀሱት ነጥቦች ላይ እለቱን የተመለከቱ ባነሮች መሰቀላቸውን ያረጋግጡ፡፡


በGoogle Map ላይ
https://maps.google.com/?cid=14408072496157346285 ማግኘት ይቻላል፡፡

ስትመጡ መደወል ትችላላችሁ፦

+251913134524/በረከት ጉዲሳ/
+251920486685/አቅለሲያ ሲሳይ/
.
.
#አዲስአበባ #ለገጣፎ #ቢሾፍቱ #ቡራዩ #አዳማ~ቤተሰቦቻችን ተገኙ!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#2ኛ_ዓመት #የአፍሪካዋ_ማዘር_ትሬዛ #TIKVAH_ETH

"የላቀ ትውልድ ለላቀች ኢትዮጵያ"

6:00 #እንገናኝ!

ቦታው፦

R= ቅዱስ ዮሐንስ ወልደነጎድጓድ ቤተክርስቲያን (ከፒያሳ ታክሲ መያዝ ይቻላል)

T1= ከዮሐንስ ቤተክርስቲያን ወደ ጎጃም በረንዳ በሚወስደው መንገድ ሲመጡ የኢትዮጲያ ንግድ ባንክ ጎጃም በረንዳ ቅርንጫፍን ያገኛሉ፡፡ አስፓልቱን ትተው ቀጥታ የሚወስደውን ኮብልስቶን መንገድ ይዘው ይጓዙ

T2= ኮብልስቶኑን ተከትለው ቀጥታ ሲጓዙ የአስፓልት መንገድ ያገኛሉ ከዛም ወደ ቀኝ(ወደ ላይ) ይታጠፋሉ፡፡

T3= አስፓልቱን እንደያዙ ወደ ላይ ትንሽ ከፍ እንዳሉ ወደ ድርጅቱ መግቢያ ያገኛሉ፡፡

📌 በተጠቀሱት ነጥቦች ላይ እለቱን የተመለከቱ ባነሮች መሰቀላቸውን ያረጋግጡ፡፡

በGoogle Map ላይ
https://maps.google.com/?cid=14408072496157346285 ማግኘት ይቻላል፡፡

ስትመጡ መደወል ትችላላችሁ፦

+251913134524/በረከት ጉዲሳ/
+251920486685/አቅለሲያ ሲሳይ/
+2519 29 04 41 03/ፀጋዬ/
+2519 09 91 16 68
.
.
#አዲስአበባ #ለገጣፎ #ቢሾፍቱ #ቡራዩ #አዳማ~ቤተሰቦቻችን ተገኙ!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ASTU የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች እና ሰራተኞች አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል። #አዳማ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አዳማ የአዋሽ ባንክ አዳማ ሪጅን ሰራተኞች አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል።
"በአንዳንድ አካባቢዎች ሰው ችግኝ ስያልቅበት በብሩ ገዝቶ እየተከለ ነው 👏" #አዲስአበባ #ጅማ #አዳማ
#አዳማ የአዳማ 09 ቀበሌ ነዋሪዎች አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል።
#አዳማ የፈትል ሰራተኞች አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል!
#ሻሸመኔ
#ሀዋሳ
#ነቀምት
#አሰላ
#አዲስአበባ
#ሽሬ
#ደብረብርሃን
#ወላይታሶዶ
#አርባምንጭ
#ጅግጅጋ
#አዳማ
#ድሬዳዋ
#ባህርዳር
#መቐለ
#ሀረር
#ጎንደር

ከሌሎች በርካታ ከተሞች ከሚገኙ የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች የSAT ውጤት ያልጠበቁት እንደሆነ በመግለፅ ቅሬታቸው እያሰሙ ይገኛሉ። የሚመለከተው አካል ማብራሪያ እንዲሰጥበትም ጠይቀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia