TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update በታንዛኒያ የሚገኙ 541 #ኢትዮጵያውያን ሰሞኑን አገራቸው እንደሚገቡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ #ነቢያት_ጌታቸው የጉዞ ሰነድ የተሰጣቸው 541 ኢትዮጵያውያን በመጪዎቹ ቀናት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱ ተናግረዋል። ባለፈው ሳምንት የታንዛኒያ መንግሥት 1900 ኢትዮጵያውያንን ከእስር ለመልቀቅ መወሰኑን አስታውቆ ነበር። አሁን ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ተዘጋጅተዋል የተባሉት 541 ኢትዮጵያውያን የታንዛኒያ መንግሥት በምኅረት ከለቀቃቸው መካከል ስለመሆናቸው #የታወቀ ነገር የለም።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሳዛኝ ዜና‼️

በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ ኮተቤ ዩኒ ቨርሲቲ አካባቢ በግንባታ ላይ የነበረ #ድልድይ አርማታ #ተደርምሶ 12 ሰዎች #ጉዳት ደረሰባቸው፡፡ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ወደ #ሆስፒታል ተወስደዋል። በአደጋው #ህይወቱ ያለፈ ሰው ስለመኖሩ #የታወቀ ነገር የለም።

Via EBC
ፎቶ፦m & jes(tikvahethiopia)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 73 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ!

ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 2,844 የላብራቶሪ ምርመራ ሰባ ሶስት (73) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 655 ደርሷል፡፡

ቫይረሱ የተገኘባቸው 49 ወንድ እና 24 ሴት ሲሆን የዕድሜ ክልላቸው ከ6 እስከ 75 ዓመት ውስጥ ይገኛል። በዜግነት 67 ሰዎች ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ ቀሪዎቹ የተለያዩ 6 ሀገራት ዜጎች ናቸው።

ቫይረሱ የተገኘባቸው 56 ሰዎች ከአዲስ አበባ (13 ሰዎች በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላቸው፣ 12 ሰዎች የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ ያላቸው እና 31 ሰዎች የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር የታወቀ ግንኙነት የሌላቸው) ፣ 4 ሰዎች ከትግራይ ክልል (ሁሉም የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው)፣ 2 ሰዎች ከአማራ ክልል (በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላቸው)፣ 8 ሰዎች ከሶማሌ ክልል (የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ ያላቸው) እንዲሁም 3 ሰዎች የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው ድንበር ተሻጋሪ መኪና አሽከርካሪዎች ናቸው።

የዕለቱ ታማሚዎች የጉዞ ታሪክና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ያላቸው ግንኙነት ፦

• የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው - 27

• በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር የታወቀ ግንኙነት ያላቸው - 15

• የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ እና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር #የታወቀ ግንኙነት የሌላቸው - 31

ተጨማሪ መረጃ ፦

በትላንትናው ዕለት ሰባት ( 7) ሰዎች (4 ከደቡብ ክልል፣ 2 ከትግራይ ክልልና 1 ሰው ከአዲስ አበባ) ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 159 ደርሷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia