TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ክላሲ ውሀ⬆️

ክላሲ የታሸገ ውሃ በጤና ላይ #ጉዳት የሚያደርስ መሆኑ በመረጋገጡ ህብረተሰቡ ጥቅም ላይ እንዳያውለው የንግድ ሚኒስቴር አሳሰበ።

የሚኒስቴሩ የገበያና ኢንስፔክሽን ዳይሬክተር አቶ ካሳሁን ሙላት እንደተናገሩት፥ በላይ ኢንዱስትሪያል ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የሚያመርተው ክላሲ የታሸገ ውሃ በጤና ላይ ጉዳት የሚያደርስ መሆኑ ተረጋግጧል።

ከ2007 እስከ 2009 ዓመተ ምህረት በተደረገ የጥራት ፍተሻ ምርቱ በተደጋጋሚ የጥራት ጉድለት የታየበት በመሆኑ እንዲታገድና ከገበያ #እንዲሰበሰብ መደረጉንም ነው ዳይሬክተሩ ያስታወሱት።

ድርጅቱ የምርት ጥራቱን እንዲያስተካክል የውዴታ ግዴታ እንዲፈርም በመደረጉ ማስተካከሉ ተረጋግጦ ታህሳስ 2009 ዓ.ም እገዳው ተነስቶለት ወደ ስራ ገብቷል።

ሚያዚያ 2010 ዓመተ ምህረት በተደረገ የገበያ ኢንስፔክሽን ስራ የምርቱ ናሙና ተወስዶ በተደረገው የቤተ ሙከራ ፍተሻ የታሸገ ውሃው በድጋሚ የጥራት ደረጃውን ያላሟላ ሆኖ ተገኝቷል።

በመሆኑም ህብረተሰቡ ክላሲ የታሸገ ውሃን ከመጠቀም #እንዲቆጠብ የንግድ ሚኒስቴር ለfbc በላከው መግለጫ አሳስቧል።

©FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia