TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ🔝

በተማሪዎች መካከል ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር በሚያነሳሱ አካላት ላይ መንግስት አስፈላጊውን #እርምጃ ሊወስድ እንደሚገባ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጠየቁ።

ተማሪዎች የተሳሳተ መረጃን ሳያረጋግጡ ለሌሎች ከማስተላለፍ ተግባር መቆጠብ እንደሚገባቸውም የሐይማኖት አባቶች አስገንዝበዋል።

በዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች መካከል ሰሞኑን በተፈጠረው አለመግባባት ዙሪያ ከተማሪዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር  ትናንት በዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ ውይይት ተካሄዷል፡፡

በውይይቱ ከተሳተፉት መካከል የ2ኛ ዓመት የማኔጅመንት ተማሪ ሐና ይመር እንደገለፀችው በተቋሙ ሁከትና ግርግር የሚፈጥሩ አካላት የማንኛውንም ብሔር እይወክሉም፡፡

”የተከሰተው ችግርም የግል ጥቅማቸውን ለማሳካት ያሰቡ ሐይሎች ተግባር እንጂ የተማሪው ፍላጎት ባለመሆኑ ድርጊቱን እናወግዛለን” ብላለች።

በግቢው ጸብ ሲፈጠር ወደ ቡድንና #ብሔር የመቀየሩ ነገር እየጎለበተ ስለሚገኝ ተማሪው ከዚህ ዓይነቱ ተግባር #ሊቆጠብ እንደሚገባም ጠቁማለች፡፡

ተቋሙም በትምህርታቸው ተገቢውን ውጤት ሳያገኙ ተሰናብተው እያለ ተመዝግበው የሚገኙ ተማሪዎችና  #በጥበቃ ስራ ላይ አድሏዊ አሰራር የሚፈጽሙ የጸጥታ ሐይሎችን ተግባር መገምገም እንደሚገባው ተናግራለች።

”ወንጀለኛ ተማሪ ብሔርን #አይወክልም፤ ጥፋት የፈጸሙ የየትኛውም ብሔር ተማሪዎች ለህግ መቅረብ አለባቸው” ያለው ደግሞ የዘንድሮ ተመራቂ ተማሪ ፉዓድ መሀመድ  ነው፡፡

ተማሪዎችም ሰላማዊ የመማር ማስተማር ስራን ለማደፍረስ የሚጥሩ አካላትን ተግባር ማውገዝና የህግ የበላይነትን የማስከበር ስራን ማጠናከር እንደሚገባቸው አሳስቧል፡፡

የ3ኛ ዓመት የህግ ተማሪ ሙፍቲ መንዛ እንደተናገረው ተግባሩ በአገሪቱ የተጀመረውን የለውጥ እንቅስቃሴ ለማደናቀፍ የታቀደ ሴራ በመሆኑ ተማሪው ተግባሩን ማውገዝ ይገባዋል፡፡

”ዩኒቨርሲቲውም አመራሩ፣ አገልግሎት ሰጪውና ሌሎች አካላት በተማሪዎች መካከል መከፋፈል እንዲፈጠር ምክንያት የሚሆኑ አሰራሮችን ሊገመግም ይገባል” ብለዋል።

የውይይቱ ተሳታፊ የሐይማኖት አባት መላዓከ ሰላም ማንደፍሮ በበኩላቸው “ተማሪው የሀይማኖት አባትና የአገር ሽማግሌዎች የሚያስተላልፉትን መልዕክት በተግባር ማዋል ይገባል፤ በተለይ ደግሞ  ተማሪዎች የተሳሳተ መረጃን ሳያረጋግጡ ለሌሎች ከማስተላለፍ መቆጠብ አለባቸው” ሲሉ ገልፀዋል፡፡

”በተማሪዎች መካከል ልዩነትን የሚፈጥሩ አካላት ተግባር የሐይማኖት አባቶች ያወግዛሉ” ያሉት ደግሞ ሼህ አብዱለጢፍ መታን ናቸው፡፡

ተማሪዎችም ቀያቸውን ለቀው ለመጡለት የመማር ማስተማር ዓላማ ቅድሚያ ሰጥተው እኩይ ተግባራትን በጋራ መዋጋት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል፡፡

በውይይቱ ላይ  የተገኙት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የርዕሰ መስተዳድሩ የክልልና የፌዴራል ግንኙነት አማካሪ አቶ #ባዘዘው_ጫኔ እና የብረታ ብረት እና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱላዚዝ መሐመድ በተቋሙ በተከሰተው የጸጥታ ችግር ማዘናቸውን ገልፀዋል፡፡

ድርጊቱ እንዳይባባስ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ የግቢው ማህበረሰብ፣ የጸጥታ አካላትና ተማሪዎች ምስጋና አቅርበዋል።

በቀጣይም ተግባሩ የተማሪዎች አለመሆኑን በመረዳት ሁሉም የተቋሙ ተማሪ አንድነትን በማጠናከርና አኩሪ እሴቶችን በማጎልበት እኩይ ተግባሮች መታገልና የፍቅር መቻቻልና የይቅርታን ባህልን ማዳበር እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ተወካይ ፕሬዝዳንት ዶክተር #ጀማል_ዩስፍ ችግሩ የተፈጠረው በአገሪቱ የተጀመረውን ለውጥ የማይፈልጉ አካላት በተማሪዎች መካከል ልዩነት በመፍጠር የራሳቸውን ዓላማ ለማሳካት ያቀዱት ሴራ መሆኑን ገልፀዋል።

ተማሪዎችም በአመራሩም ሆነ በጸጥታ አስከባሪ ሐይሎች ላይ ያነሷቸው ችግሮችን ለመፍታት ዩኒቨርሲቲው ከምንጊዜውም በላይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡

የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ የጥፋቱ አካል የሆኑ ተማሪዎች በህግ እንደሚጠየቁም ተናግረዋል፡፡

በውይይቱ የተቋሙ፣ የፌዴራልና የክልል ተወካይዎች፣ የሐይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌሎች፣ የጸጥታ አካላትና ተማሪዎች የተገኙ ሲሆን በእለቱም እርስ በርስ ተጋጭተዋል የተባሉት ተማሪዎች #እርቅ ፈጽመዋል።

በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 11 ቀን 2011 ዓ ም ከምሽቱ 1 ሰዓት በተከሰተ አለመግባባት በአምስት ተማሪዎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሜቴክ ይቅርታ መጠየቅና እርቅ ማውረድ እንደሚፈልግ አስታወቀ‼️
.
.
"ይቅርታ መጠየቅና #እርቅ ማውረድ ካለበት አካል ጋር ሁሉ ይህንን ያደርጋል"

"መልዐክ ሆኖ ቢመጣ ሰው #ሰይጣን በሚል እንደሚያነበው አውቆ ስሙን ይቀይራል"
.
.
የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፓሬሽን/ሜቴክ/ይቅርታ መጠየቅና #እርቅ ማውረድ ካለበት አካል ጋር ሁሉ እንደሚያደርግ የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ብርጋዴር ጀነራል #አህመድ_ሀምዛ አስታወቁ፡፡

ብርጋዴር ጀነራል አህመድ ሀምዛ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንገለጹት፤ ሜቴክ ከሥራ አጋሮቹ ጋር የነበረው ግንኙነት የተበላሸና በጸብ የተሞላ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት ይቅርታ መጠየቅና እርቅ ማውረድ ካለበት አካል ጋር ሁሉ ይህንን ይፈጽማል፤ ተቋሙም የህዝብ እንደመሆኑ ከዚህ በኋላ ሚስጢር አይኖረውም፤ እቅዶች ድረ ገጾች ላይ ይቀመጣሉ፤ ለመገናኛ ብዙኃንም ክፍት ይሆናል ብለዋል።

ተቋሙ አብረውት ከሚሰሩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶችን እያደረገ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፣ ‹‹አገልግሎት ሰጪ እስከ ሆንን ድረስ ከአገልግሎት ፈላጊው ዝቅ ብሎ ነው መታየት ያለብን›› ብለዋል፡፡ ደንበኞች ለከፈሉት ገንዘብ እንኳን አገልግሎት ሲጠይቁ ይሰጣቸው የነበረውምላሽ በጣም አደገኛና በጸብ የተሞላ እንደነበር በማስታወስ ይህንን ሁኔታ ለመቀየርም እንደሚሰራ አብራርተዋል።

ስኳር ኮርፖሬሽንን ለአብነት በመጥቀስም ከኮርፓሬሽኑ ጋር የነበረው ግንኙነት ጥሩ እንዳልነበረ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ኮርፖሬሽኑ በጣም ከፍተኛ ገንዘብ ከፍሏል፤ ተቋሙ ግን ጨርሶ ያስረከበው አንድም ፕሮጀክት የለም፡፡ ፕሮጀክቶቹን ካለማጠናቀቅም በላይ አንዳንዶቹን ወገብ ወገባቸው ላይ እያደረሰ ነው በሀይል እንዲረከቡ ያደረገው›› ሲሉ ያብራራሉ።

በሌላ በኩል መልካም ስምን ከመገንባት አንጻር አደረጃጀቱን መቀየር ያስፈልጋል ያሉት ብርጋዲዬር ጀነራል አህመድ ፣ ‹‹ሜቴክ ከአሁን በኋላ መልዐክ ሆኖ ቢመጣ እንኳ ሰው ሰይጣን ብሎ ስለሚያነበው ስሙን መቀየር አስፈልጓል››ብለዋል፡፡ ይህንን ለማከናወንም መረጃዎችን የማሰባሰብ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

መረጃ የማሰባሰብ ስራው ከተጠናቀቀ በኋላም በጥቂት ጊዜ ውስጥ አደረጃጀቱንና ስሙን በመቀየር በአዲሱ ስሙም አዲስ ሆኖ እንደሚቀርብና እንደ ማንኛውም የልማት ድርጅት ህግን ተከትሎ መስራት እንደሚጀምር አስታውቀዋል።

በአሁኑ ወቅት በስድስት ወራት ውስጥ ተሰርቶ የሚጠናቀቅ የሪፎርም እቅድ መዘጋጀቱን ገልጸው፣ ይህ እቅድ ሲዘጋጅ ይሳካሉ ተብለው ከተቀመጡ ግቦች መካከል ዋናው የተቋሙን የጠፋ ስም መመለስ፣ በህግና ስርዓት ብቻ ተከትሎ እንዲሰራ ማድረግ የሚሉት ዋና ዋናዎቹ መሆናቸውን አብራርተዋል።

ምንጭ፦ አዲስ ዘመን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 21/2011 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ መንግስት “የጤፍ ባለቤት ነኝ” ያለውን የሆላንድ ድርጀት በዓለም አቀፉ የግልግል ፍርድ ቤት ሊከስ ነው።
.
.
በደቡብ ክልል አማሮ ወረዳ ሁለት አርሶ አደሮች በኦሮሞ ነፃ አውጪ ግንባር "ኦነግ ታጣቂዎች" መገደላቸውንና አንድ አርሶ አደር መቁሰሉን የአከባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
.
.
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር የሴፍቲና ሲኬዩሪቲ ዲፓርትመንት ባለሙያዎች በባቡሩ ላይ #ድንገተኛ የእሳት አደጋ ቢከሰት እንዴት መቆጣጠር እንደሚቻል የሚያሳይ ልምምድ አካሂደዋል።
.
.
ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው እለት የቀጠለውን የሚኒስትርና ተጠሪ መስሪያ ቤቶችን የ100 ቀን እቅድ አፈፃፀም ግምገማ መርተዋል።
.
.
የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፓሬሽን/ሜቴክ/ይቅርታ መጠየቅና #እርቅ ማውረድ ካለበት አካል ጋር ሁሉ እንደሚያደርግ የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ብርጋዴር ጀነራል #አህመድ_ሀምዛ አስታውቀዋል።
.
.
በሰቆጣ ከተማ ሦስት #ፓኪስታናውያን በሕገ ወጥ የሞባይል ሽያጭ ተሰማርተው እጅ ከፈንጅ ተይዘዋል።
.
.
በአዲስ አበባ ከተማ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ሰርተፍኬት፣ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ፣ የልደትና ሞት ሰርተፍኬት እንዲሁም የጋብቻ እና ፍቺ ሰርተፍኬቶች በዲጂታል ሰርተፍኬት ሊቀየሩ ነው ተብሏል።
.
.
ኢ/ር #ታከለ_ኡማ ቦሌ አራብሳ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ የፈረሰውን መስጂድ በመጎብኘት የአከባቢውን የሙስሊም ማህበረሰብም አነጋግረዋል፡፡
.
.
#የፌዴራል_መንግሥት አመራሮች የድሬዳዋ ነዋሪዎችን በከተማዋ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ አወያይተዋል፡፡
.
.
በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና በማህበራዊ ፍትህ ላይ ያተኮረ የመጀመሪያውን አረንጓዴ የፖለቲካ ፓርቲ (Green Party) ለማቋቋም ጊዜያዊ አስተባባሪ ፓርቲ መሰየሙን ዋዜማ ራድዮ ዘግቧል።
.
.
ከሳውዲ አረቢያ ጋር በተደረገው የሁለትዮሽ ስምምነት መሰረት በህጋዊ መንገድ ለሚሄዱ ሰራተኞች የቪዛ አገልግሎት መሰጠት መጀመሩን የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል።
.
.
ግምታዊ ዋጋው 400 ሺህ ብር የሚያወጣ የባህርዛፍ አጠና ያለምንም ህጋዊ ሰነድ ከአገር ሊወጣ ሲል #በጅግጅጋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት መያዙን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል።
.
.
ከጥር 19 እስከ 21 ለተከታታይ ሦስት ቀናት #በሀዋሳ_ከተማ ሲካሄድ የቆየው የኢህአዴግ ወጣቶች ሊግ 4ኛ ድርጅታዊ ጉባዔውን ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበሩን በመምረጥ ተጠናቋል።
.
.
ከጭናግሰን ከተማ የማርያምን ክብረ በዐል አክብረው ይመለሱ በነበሩ ምዕመናን ላይ ወጣቶች መንገድ መዝጋታቸውን ተከትሎ #በጅግጅጋ_ከተማ ተፈጥሮ የነበረው ግጭት መረጋጋቱ ታውቋል። በግጭቱ የ2 ሰው ህይወት አልፏል።
.
.
ቀዳማዊት እመቤት #ዝናሽ_ታያቸው የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ለተከታተሉበት የጎንደሩ ጻዲቁ ዮሐንስ 1ኛ ደረጃ ሙሉ ሳይክል ትምህርት ቤት የኮምፒዩተር ድጋፍ አድርገዋል፡፡
.
.
#በድሬዳዋ_ከተማ የትራንስፖርትና የግብይት #አድማ ለማድረግ ያቀዱ ነዋሪዎች ከድርጊታቸው ይቆጠቡ ዘንድ #የምስራቅ_ዕዝ_ጠቅላይ_መምሪያ አስጠነቅቋል።
.
.
አቃቤ ሕግ የቀድሞ #የሜቴክ የስራ #ሀላፊዎች በነበሩት ሻለቃ #ክንደያ_ግርማይና ሌተናል ኮሎኔል #አሰፋ_ዮሐንስ ላይ ክስ መስርቷል።
.
.
የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ) በዚህ ሳምንት ሐሙስ በይፋ ትጥቅ ይፈታል።
.
.
በቅርቡ በመንግስት እና ኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) መካከል በአምቦ በተደረገው ስምምነት መሠረት እርቁን ተግባራዊ ለማድረግ የተመረጠው የቴክኒክ ኮሚቴ ሥራውን በተግባር መጀመሩን የቴክኒክ ኮሚቴው አባል አቶ #ጀዋር_መሀመድ አስታውቀዋል።
.
.
ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ #ዝናሽ_ታያቸው ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የህክምናና የኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ መሳሪያዎችን ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልና ለሁለት ትምህርት ቤቶች ድጋፍ አድርገዋል።
.
.
#የኢፌዲሪ_አየር_ሃይል በሶማሊያ ከባይደዋ በስተምስራቅ 75 ኪሎ ሜትር ላይ ቡርሃይቤ በተባለ የአልሻባብ ይዞታ ላይ ጥር 16 ቀን 2ዐ11 ዓ.ም ድብደባ በመፈፀም ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረሱን የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።
.
.
ሰሞኑን በድሬዳዋ ከተማ የተከሰተዉን #አለመረጋጋት ተከትሎ የከተማዉ ፖሊስ ኮሚሽን 308 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አዉሎ ምርመራ እያካሄደ ነዉ፡፡

ምንጭ፦ ዋዜማ ራድዮ፣ etv፣ fbc፣ VOA፣ ኢዜአ፣ ኢ.ፕ.ድ፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት፣ የጠ/ሚ ፅ/ቤት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ አብመድ
.
.
ሰላም እደሩ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#OROMIA #Peace

" . . . እርቁ በምንፈልገው ፍጥነት አለመምጣቱ ቢያሳዝንም ተስፋ መቁረጥ ግን አያስፈልግም " - አቶ ጃዋር መሀመድ

አቶ ጃዋር መሀመድ የኢፌዴሪ መንግሥትና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (OLA) በታንዛኒያ ዳሬሰላም ያደረጉት የሁለተኛው ዙር ድርድር ያለ ስምምነት ከተበተነ በኃላ ድርድሩን በተመለከተ ሰፋ ያለ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

አቶ ጃዋር መሀመድ ምን አሉ ?

- መንግስትንና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (WBO-OLA) ለማስታረቅ የተደረገው 2ኛው ዙር ሙከራ አለመሳካቱ በህዝቡ ዘንድ ትልቅ ሀዘን የፈጠረ ነው።

- በሕዝቡ በኩል ቢያንስ ሁለቱም ወገኖች በዚህ ዙር የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንደሚደርሱ ተስፋ ተደርጎ ነበር። በተለይ የጦር አዛዦች ከጦር ሜዳ ለውይይት መምጣታቸው እርቀ ሰላሙን ያሳካል የሚል ተስፋ ፈጥሮ ነበር።

- ድርድሩ አለመሳካት እንደ ትልቅ ውድቀት ሲቀርብ እናያለን ነገር ግን ውይይቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ብዙ ርቀት ተጉዟል። እርቅ ከማያስፈልግበት ወይም ከማይቻልበት ደረጃ ተነስተን የሁለቱም ወገን አመራሮች ፊት ለፊት ተገናኝተው መወያየት ደረጃ ደርሰናል።

- ይህ እርቅ በምንፈልገው ፍጥነት አለመምጣቱ ቢያሳዝንም ተስፋ መቁረጥ ግን አያስፈልግም። ተስፋ ልንቆርጥም አንችልም። ሌላ መፍትሄ የለንምና። ስለዚህ የሰላም ድርድሩ እንደሚቀጥል ተስፋ እናደርጋለን።

🕊አቶ ጃዋር መሀመድ በሁለተኛው ዙር የሰላም ድርድር ላይ ከተሳተፉት አካላት እና ከተለያዩ ምንጮች ተረዳሁት ያሉትንና ለቀጣይ ዙር የሰላም ድርድር ያግዛሉ ያሏቸውን ሃሳባችን በዝርዝር አቅርበዋል።

➜ በሁለተኛው ዙር የሰላም ድርድር ሁለቱም ወገኖች በእውነት #እርቅ/#ሰላም ለመፍጠር ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ።

በዚህ የተነሳ ሁለቱም ወገኖች ልክ እንደ ህዝቡ ይህ ምዕራፍ በእርቅ ስምምነቱ ይጠናቀቃል የሚል ተስፋ (expectation) ይዘው ነበር የቀረቡት።

ሁሉም ተሳታፊዎች (WBO / የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ፣ መንግስት እና አሸማጋዮች) በሰላም፣ በእርቅ ይጠናቀቃል የሚል ተስፋ ይዘው ስለሄዱ ግባቸው ላይ ባለመድረሳቸው የመናደድ ስሜት ውስጥ ገብተዋል። በዚህ ምክንያት ለቀጣዩ የሰላም ውይይት በር ከመክፈታቸው በፊት ተለያይተዋል።

➜ ሁለቱም ወገኖች በቅን ልቦና ለመታረቅ ቢሄዱም፣ አንዱ ከአንዱ የሚፈልገውን (demands/concessions) ለመስጠት እና ለመቀበል ሙሉ በሙሉ የተዘጋጁ አይመስሉም።

በመጀመሪያው ዙር እርስ በርሳቸው የሚፈልጉትን ነገር ተረድተው ተለያይተዋል። በሁለተኛው ዙር ደግሞ አንዳቸው ለሌላው መስጠት የማይችሉትን ያወቁ ይመስለኛል።

አሁንም ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቁርጠኝነት ካላቸው፣ ቀጣዩ እርምጃ ሁለቱም ወገኖች ጥያቄዎቻቸውን ለማስተካከል (modifying demands) መዘጋጀት አለባቸው። ይህ ማለት እንዱ መቀበል የማይችላቸው ነገሮች ላይ በመግፋት መጋጨት መተው አለባቸው።

በሰላም ድርድር ውስጥ የሚፈልጉትን እና ይገባኛል ብለው የሚያስቡትን ሁሉ ማግኘት አይቻልም። ይገባኛል ብለው የሚያስቡትን ሁሉ ማጣትም አይቻልም። ሁለቱም ወገኖች ወደ መካከለኛው አቋም መምጣት ይጠበቅባቸዋል።

➜ የሰላም ድርድሩ ዋነኛው #እንቅፋት እየሆነ ያለው ዋና ምክንያት አንዱ ከአንዱ የሚፈልገው ነገር ላይ ተራርቀው ነው ብዬ አላስብም። ትልቁ እንቅፋት #አለመተማመን ነው። በሁለቱ ወገኖች በታሪክ ካለው ግንኙነት እና ከአገራችን የፖለቲካ ባህል አንፃር አለመተማመናቸው ይጠበቃል። የውጪው አካል ያስፈለገበትም ምክንያት ይሄ ችግር ስለተረዳ ነው። እነዚህ አስታራቂዎች የእርቅ ስምምነት ላይ መድረስ ብቻ ሳይሆን የስምምነቱ አፈጻጸምን ለማረጋገጥ ኃላፊነቱን እንደሚወስዱ ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ይህንን አሻሚ የሆነ ችግር ለማሻሻል ይጠቅማል።

➜ ከውስጥ ከውጭ " እርቅ ሊመጣ ነው " ብለው እያዘኑ የነበሩት ወገኖች አሁን በመፍረሱ በደስታ እየፈነደቁ ነው። ሌላ ዙር ድርድር እንዳይደረግም እያሴሩ ነው። የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (OLA) እና የመንግስት አመራሮች አሁንም ጉዳዩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል አቋም ካላቸው እነዚህ ፀረ-ሰላም ኃይሎች ወደ ውስጥ እንዳይገቡ ሁሉንም ክፍተቶች መዝጋት አለባቸው። በተጨማሪም የሚቀጥለውን ዙር እድሎች ከሚያጠብ ወይም ከሚያርቁ ድርጊቶች እና ቃላት መቆጠብ አለባቸው። ይህም የሚዲያ ፕሮፓጋንዳ እና የመስክ ውጊያን አለማባባስን ያካትታል።

➜ እኔ እስከተረዳሁት ድረስ ከ2ቱም ወገን ደጋፊዎች በኩል የነበረው የ " #ምታ - #ስበር - #አጥፋ " ዘመቻ ባለፉት አመታት በጣም መቀነሱን ነው። የእርቅ ሀሳብ መደገፍ እና ሰላም እንዲወርድ ያላቸው ምኞትም ከየትኛውም ጊዜ በላይ እያደገ መጥቷል።

➜ አሁንም የሁለተኛው ዙር ሙከራ ስላልተሳካ እርስ በርስ ጣት መቀሳሰር እና መደማማት ምንም ፋይዳ እንደሌለው መረዳት ያስፈልጋል። የሚጠቅመው የሚደግፉትን ወገኖች ወደ ድርድሩ እንዲመለሱ እና የሚጠበቅባቸውን እንዲሰጡ ማበረታታት እና ጫና ማድረግ ነው።

➜ በመጨረሻም ፤ ልብ ሊባል የሚገባው ነገር ይሄ የሰላም ድርድር የጦር ሜዳ ውጤቶች አይደለም።

ሁለት የሚዋጉ ወገኖች ለእርቅ ድርድር የሚቀመጡት በሁለት ሁኔታዎች ውስጥ ነው።

የመጀመሪያው ፦ በጦር ሜዳ ላይ አንደኛው የበለጠ የበላይነት አግኝቶ ወደ ድል ሲቃረብ እና ሌላኛው ወገን ሙሉ በሙሉ ከመሸነፉ በፊት ለመታረቅ ሲወስን ነው።

ሁለተኛው ፦ ከረዥም ጊዜ ጦርነት በኋላ ሁለቱም ወገኖች መሸናነፍ ካልቻሉ ነው። በWBO-OLA እና በመንግስት መካከል ያለው ጦርነት የመሸናነፍ ወይም የመድከም ደረጃ ላይ አልደረሰም። በአጭር ጊዜ ውስጥም እዚህ ደረጃ ላይ ይደርሳል ብዬ አላስብም። ይህ ውይይት የመጣው በህዝብ እና በአለም አቀፍ ማህበረሰብ ግፊት ነው።

በተለይም ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በሀገራችን ሰላም እንዲሰፍን ያሳየው ትኩረት ያልተጠበቀ እና ትልቅ እድል ነው።

የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ትኩረት በፍጥነት እየተቀየረ ነው። ስለዚህ ፤ ጉዳያችን ትኩረት ባገኘበት በዚህ ወቅት በፍጥነትና በብልሃት መጠቀም አስፈላጊ ነው። ይህንን እድል መጠቀም ካልቻልንና የሚባክን ከሆነ ለረጅም ጊዜ እንቆጫለን።

#JawarMohammed

Via https://publielectoral.lat/tikvahethAFAANOROMOO

#TikvahEthiopiaAFAANOROMOO

@tikvahethiopia