TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሰላምን ባህል ማድረግ የሰላም ጥቅምን በመገንዘብ ለሰላም ምቹ የሆኑ ነገሮችን ለይቶ በትኩረት መንቀሳቀስ ሲቻል ነው፡፡

ሰላም ካለ፡-
• ለውጥና እድገት ማምጣት፤
• ከአድሏዊ አሰራር ነጻ መሆን፤
• ግጭትን በውይይት መፍታት፤
• ከማህበራዊ መፈረካከስ ወደ አንድነት መምጣት፤
• ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎን ማሳደግ፤
• ነፃ አስተሳሰብን ማዳበር፤
• የተፈጥሮ ደህንነትን ማረጋገጥ ይቻላል፡፡

ሰላማችን ህልውናችን ነው
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update CNN⬆️

ዓለም አቀፉ ብዙኃን መገናኛ ሲኤን ኤን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶር. ዐብይ አህመድን
በተመለከተ ሰፊ ትንታኔ አስነብቧል፡፡

#ወጣቱ#ዲሞክራቱ እና #ሰላምን ሰባኪዉ መሪ ኢትዮጵያዉያን ለዘመናት ሲመኙት የነበረ አይነት መሪ መሆኑ በዘገባዉ ተገልጿል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን በመምጣታቸዉ ኢትዮጵያን ከእርስ በርስ ግጭት እና መበታተን ታድገዋል፡፡

በአስተዳደር ቆይታቸዉም እስረኞች ተለቀዋል፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ሰላም ፈጥረዋል፣ የሚዲያ ነፃነትን አዉጀዋል፣ አስቸኳይ አዋጁን አንስተዋል፣ ኢኮኖያዊ ለዉጦችን የተመለከቱ ዉሳኔዎችን አሳልፈዋል፡፡ ከሁሉም በላይ የኢትዮጵያዉያንን ተስፋ አለምልመዋል ብሏል ዘገባዉ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተወዳጅነታቸዉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ጠቅሶ በሃገሪቱ መዲና የጠቅላይ ሚኒስትሩን ምስሎች እና እሳቸዉን የሚደግፉ መልዕክቶች መኪኖች ላይ እና በማህበራዊ ሚዲያዎች ማየት የተለመደ ነዉ ብሏል፡፡ ምስላቸዉን የያዙ ቲሸርቶችም ይሸጣሉ ሲል ገልጿል፡፡

ዶ.ር ዐብይ ከሳቸው በፊት ከነበሩት መሪዎች ልዩ ናቸው ያለዉ #ዘገባዉ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትን በፍቅር ይቀበላሉ፣ ከአድናቂዎቻቸው ጋር #ፎቶግራፍ ይነሳሉ፣ ፈገግታቸውም ለካሜራ ሳይሆን #ከልብ ነው ሲል አስፍሯል፡፡

ቶም ጋርድነር የተሰኘ እንግሊዛዊ ጋዜጠኛን ዋቢ አድርጎ ዘገባዉ እንዳሰፈረዉ ዶር. ዐብይ ከፈጣሪ የተላኩ መሪ ተደርገዉ እንደሚቆጠሩ ገልጿል፡፡

የተወሰኑ የማህበረሰብ ክፍሎች ነብይ እንደሆኑ ያምናሉም ብሏል፡፡ ዶር. ዐብይ የመበታተን ስጋት ተጋርጦባት የነበረችዉን ሀገር መታደግ ችለዋል ፡፡

መሪዉ #በወታደራዊ አስተዳደር በቂ ልምድ ማካበታቸዉን እና ይህም እንደጠቀማቸዉ አስነብቧል።

ሲኤን ኤን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ደህንነት እና በተለያዩ አካባቢዎች የሚነሱ የመንጋ ፍትህ እንዲሁም ሁከቶች ጥንቃቄ ያሻችዋል ብሏል፡፡

እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ሀገራት ዶር. ዐብይን የመሰሉ ሰዎች ከሚሊየን አንድ ናቸዉ ያለዉ ዘገባዉ አፍሪካ ካፈራቻቸዉ ጥቂት ታላቅ መሪዎች አንዱ ሊሆኑ ይችላሉ ሲል ትንታኔዉን ደምድሟል፡፡

ምንጭ፦ ሲኤን ኤን (በአመብድ ወደ አማርኛ ተቀየረ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወገን! ሰከን ማለት ዋጋ አለው! #ሰላምን እስክታጣት ድረስ ምንም ላይስመስልህ ይችላል። ነገር ግን ሰላም አንዴ ከእጅህ ከወጣች የልጅ ልጅህን #ብትገብር እንኳን መልሰህ ላታገኛት ትችላለህ።

#ሶሪያ የቀደመው ገፅታዋን እና #አሁን ያለውን ገፅታዋን ከላይ ባለው ፎቶው ተመልከት። ያኔ በትንሽ በትልቁ አትባላም።

ሰላም ለኢትዮጵያ!
ተወያይተን ችግራችንን እንፍታ!
#ETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
‹‹ሰላም በአጠገባችን ያለ ግን የማንገዛው፤ ካልጠበቅነው ግን የሚጠፋ ነው፡፡ በመንግሥት በኩል ትኩረት ሰጥተን ሰላምን ለመጠበቅ እንሠራለን፡፡ ግን ወጣቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና አባ ገዳዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ሴቶች፣ በጋራ #ሰላምን እንድንጠብቅ ጥሪየን አቀርባለሁ››

▪️▪️ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ - ሀዋሳ▪️▪️

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወገን! ሰከን ማለት ዋጋ አለው! #ሰላምን እስክታጣት ድረስ ምንም ላይስመስልህ ይችላል። ነገር ግን ሰላም አንዴ ከእጅህ ከወጣች የልጅ ልጅህን #ብትገብር እንኳን መልሰህ ላታገኛት ትችላለህ።

#ሶሪያ የቀደመው ገፅታዋን እና #አሁን ያለውን ገፅታዋን ከላይ ባለው ፎቶው ተመልከት። ያኔ በትንሽ በትልቁ አትባላም።

ሰላም ለኢትዮጵያ!
ተወያይተን ችግራችንን እንፍታ!
#ETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"መቐለ ዩኒቨርሲቲን አመስግኑልኝ!
በአማራና በትግራይ ህዝቦች መካከል #ሰላምን ለማምጣት እንዴት ሰላማዊ ውይይት ማድረግ እንደሚቻል ጉባኤ አዘጋጅቷል፡፡ ተቋማት ለህብረተሰቡ ጥቀምና በጋራ መግባባት ላይ የተመሠረተ ህይወት እንዲኖረው ለማድረግ ሀላፊነት ያለባቸው ቢሆንም እስካሁን ዝምታ ውስጥ ነበሩ፡፡ ሌሎች አማራ ክልል ውስጥ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎችም ይህንን እንደሚያደርጉ ተስፋ አለኝ፡፡"

via~Bekal Alamirew
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ኡስታዝ ከሚል ሸምሱ ፦

" ውድ ወንድሞች እና እህቶች እኛ እንደ ሙስሊሞች በቁርአን ፣ በሀዲስ ነው የምንመራው።

አላህ ሱብሀነ ወተአላ በራሳችን ፣ በስሜታችን ፣ በነብስያችን እንድንመራ አልፈቀደልንም። የመልካም ስራዎች ተምሳሌት ፤ የመልካም ተግባራት አርአያዎች እንጂ እኛ ከሌሎች ሰዎች መጥፎ ነገሮችን የምንኮርጅ ፤ መጥፎ ነገርን በመጥፎ የምንመልስ ሰዎች አይደለንም።

አላህ በቁርአን " ክፉ ነገርን በመልካም መልስ ያ ነው በአንተ እና በሌሎች መካከል ያለን ትስስር ፤ ግንኙነት የሚያስተካክለው " ስለሚለን በስሜት ውስጥ ሆነን የምንራመድ ህዝቦች አይደለንም።

ውድ ወንድሞች ፤ እህቶች እዚህ እንዳማረብን ቀጣዩ ኢዳችንን የተሳካ ኢድ እንዲሆን ፤ የታሳቡ ነገሮች ሁላ ከሽፎ ፤ ለሀገራችን ሰላም ፣ ለሀገራችን አንድነት ፣ የሀገሪቷ ባለቤቶች መሆናችንን በተግባር የምናሳይበት ኢዳችንን በጉጉት እየጠበቅን ባለንበት ሁሉ #ሰላምን መስበክ ፣ በሰላም መኖር ፀረ ሰላም የሆኑ ሰዎችን ደግሞ እነሱ በሚፈልጉት መስመር ውስጥ ሳንገባ መሄድ አለብን።

አላህ ኢዱን የሰላም ኢድ አድርግልን፤ ኢዱን የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የክብር እና የእኩልነት ኢድ ያድርግልን። "

@tikvahethiopia
አባታዊ የደስታ መልዕክት !

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በወቅታዊ ጉዳይ አባታዊ የደስታ መልእክት አስተላልፈዋል።

ከመልዕክታቸው የተወሰደ ፦

" ውድ ወገኖቻችን ጦርነትን የሰሙ ጆሮዎቻችን ዛሬ #ሰላምን እና #እርቅን በመስማታቸው ደስታችን ወደር የሌለው መሆኑን ለኢትዮጵያውያንና ለኢትዮጵያውያት ልጆቻችን ለመግለጽ እንወዳለን።

አገራችን ኢትዮጵያን ከአስከፊ የጦርነት ታሪክ ለማውጣት፣ እግዚአብሔር በሰጣት መልካም ዕድል፣ የተፈጥሮና የሃይማኖት ሀብት እንድታድግ ሰላምን መናፈቅና የሰላም መልእክተኛ መሆን ያስፈልጋል።

ሀሳብ የበላይ ሲሆን የጦር መሣሪያ የእርሻ መሣሪያ ወደ መሆን ይለወጣል። እኛም በተደጋጋሚ የሰላም ጥሪያችንን እያስተላለፍን የቆየን እንደመሆኑ መጠን በዚህ መልካም የምሥራች ደስ ብሎናል።

አሁንም ኢትዮጵያውያን በሙሉ አገሩ የሁላችን ነውና ልንጠብቀው፤ አለመግባባታችንን በውይይት ልንፈታው ፤ ቃላችንን ከመሬት ላይ አሳርፈን እርቁን እውነተኛ ልናደርገው ይገባናል።

#ወጣቶች ሲሞቱ ሳይሆን ተምረው ሲመረቁ ፤ ተዋደው ጋብቻ ሲመሠርቱ ለማየት እንናፍቃለን።

የተዘጉ ደጆች ሁሉ በምሕረት እንዲከፈቱ ፤ የተጨነቁ ሁሉ ፀሐይ እንዲወጣላቸው በብርቱ እንሻለን።

ለዚህ እርቀ ሰላም መምጣት በብርቱ የደከሙትን የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ አባላትንና የሰላም ጥሪ የተቀበሉት ልጆቻችንን እግዚአብሔር አምላካችን ዐስበ ሐዋርያትን እንዲከፍልልን እንመኛለን። ለሞቱት ዕረፍተ ነፍስን ለታመሙት ፍጹም ጤንነት እንዲሰጥልን እንለምናለን። "

(የቅዱስነታቸው መልዕክት ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ኦሮሚያ #ትኩረት

በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ የወለጋ አካባቢዎች አሁንም በቀጠለው የፀጥታ ችግር በርካቶች ህይወታቸው እያለፈ ፣ አካላቸው እየጎደለ፣ ንብረታቸው እየወደመ እንደሚገኝ ቤተሰቦቻችን ጠቁመዋል።

ባለፉት ዓመት ህዝቡ በሰላም እጦት ብዙ ቢሰቃይም መፍትሄ ሳይገኝ አሁንም እየተባባሰ በመቀጠሉ ንፁሃን ክፉኛ እየተጎዱ እና ስቃያቸውም እየተባባሰ እንደሚገኝ ነው ቤተሰቦቻችን የገለፁት።

ከጥቂት ቀን በፊት የፀጥታ ችግር ባለባቸው በወለጋ የተለያዩ አካባቢች ላይ #ንፁሃን እንዲጠበቁ ፣ የህዝቡ ስቃይ ትኩረት ባለማግኘቱ የሰሜን ክፍሉን ያህል ትንሽ እንኳን ትኩረት እንዲሰጠው እና ዘላቂ መፍትሄ እንዲፈለግ ቤተሰቦቻችን ተማፅኖ ማሰማታቸው አይዘነጋም።

ከሰሞኑን በተለይም በምዕራብ ኦሮሚያ በሚገኙት ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ጃርዳጋ ጃርተ ወረዳ እና በምስራቅ ወለጋ ኪረሙ ወረዳ ውስጥ በርካቶች ህይወታቸው አልፏል፣ ንብረታቸው ወድሟል ፣ #ሰላምን_ፍለጋ ሸሽተው ወደ ሌሎች አካባቢዎችም መግባታቸውን ለመስማት ችለናል።

አንድ የቤተሰባንች አባል ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ፤ " ለንፁሃን ጭፍጨፋ ፣ ለንብረት ውድመት ለዚህ ሁሉ ምስቅልቅል ተጠናቂነት መኖር አለበት " ብሏል።

" እውነት መንግስት / አስተዳዳሪ ነኝ ፤ የህዝብንም ደህንነት አስጠብቃለሁ የሚል ካለ የትኛው አካል ለሚፈጠሩት ችግሮች ምክንያትና መንገድ እየሆነ እንዳለ ፣ ማን ግፍ እየፈፀመ እንዳለና ለዚህም ድርጊት ተባባሪ እየሆነ እንዳለ ምርመራ በማድረግ ማሳወቅ አለበት ፤ በየዕለቱ ሰዎች እየረገፉ ፣ እየተፈናቀሉ ፣ እየተራቡ እያዩ ዝም ያሉት ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ከእንቅልፋቸው ነቅተው መፍትሄ እንዲመጣ ንፁሃንን ከሞት እንዲድኑ ድምፃቸውን ማሰማት መቻል አለባቸው ። " ብሏል።

የመንግስት ዋናው ስራ የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ ፤ ከየትኛውም የታጠቁ አካላት የሚደርስን ጥቃት መከላከል ፣ አጥፊዎችን መቅጣት ነው ይህን ማድረግ ባይቻል እና ንፁሃን ቢጎዱ ተጠያቂነት መኖር አለበት ሲል አክሏል።

በኦሮሚያ ክልል ባለው ፀጥታ ጉዳይ ፤ በመንግስት መዋቅር ውስጥ የሚታዩ ችግሮች መኖራቸውን ይህም በተደጋጋሚ መገለፁን ነገር ግን እስካሁን መፍትሄ እንዳልተገኘለት ገልጿል።

" ህዝብ መንግስት አለኝ ሚለው ደህንነቱ እንዲጠበቅ እንጂ በየዕለቱ ያለበት ችግር እየተባባሰ ህይወቱን እያጣ፣ እጅግ ደክሞ ያፈራው ንብረቱ እየወደመበት እንዲቀጥል አይደለም " ያለው ይኸው የቤተሰባችን አባል ባለፉት ጊዜያት እሱን ጨምሮ ቤተሰቦቻቸው በግጭት ቀጠና ውስጥ ያሉ ወገኖች ያሳለፉት ስቃይ በቃላት የሚገለፅ እንዳልሆነ አስረድቷል።

በኦሮሚያ ውስጥ የፀጥታ ችግሮች ባለባቸው ቦታዎች ስለሚደርሰው ስቃይ ብዙ ቢነገርም መፍትሄ ሳያገኝ ዛሬም የሰዎች ህይወት እየተቀጠፈ እንደቅጠል እየረገፈ ይገኛል።

የአንድ ሀገር ዜጎች ህይወታቸው በግፍ እየረገፈ እየታየ ለችግሩ መፈጠር በተለያዩ አቅጣጫዎች የተለያዩ ምክንያቶች እየተደረደሩ ፣ ጥላቻዎችም እየተሰበኩ፣ ሁኔታዎችም #ከመሻሻል ይልቅ ክፉኛ እየተባባሱ ቀጥለዋል።

ህዝቡ ሰላም ርቆት፣ ኢኮኖሚው ደቆ፣ አርሶ እንዳይበላ ሆኖ፣ እየታፈነ ሚሊዮኖች እየተጠየቀበት ፣ መውጫ እና መግቢያ አጥቶ ፣ የሚወዳቸውን እየተነጠቀ፣ ዓመታትን በገፋበት የግጭት ቀጠናዎች መፍትሄ እንዲያገኝ ግፊት ማድረግ እንደሚገባ ቤተሰቦቻችን ገልፀዋል።

@tikvahethiopia