TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#COVID19

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚያግዙ የህክምና ቁሳቁሶችን ከተለያዩ ሀገራት ወደ ቻይና እያጓጓዘ እንደሚገኝ ገልጿል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"በጅማ ኤርፖርት ፍንዳታ አልደረሰም፤ በረራም አልቆመም" - የኢትዮጵያ አየር መንገድ

በአንዳንድ የማህበራዊ ትስስር ገፆች በጅማ ኤርፖርት ፍንዳታ እንደደረሰና በረራም እንደቆመ ተደርጎ የሚናፈሰው ወሬ #ፍፁም_ሐሰት መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አረጋግጧል።

በአሁኑ ሰዓት በጅማ መደበኛ የኤርፖርት እና የበረራ ስራዎቻችን በተለመደው መልኩ እየተከናወኑ ይገኛሉ ሲልም አየር መንገዱ አሳውቋል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ

@tikvahethiopia
በአፍሪካ ቀዳሚ #EthiopianAirlines

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት ማህበር (IATA) በፋርማሲዩቲካል ሎጅስቲክስ የገለልተኛ ገምጋሚ (CEIV Pharma) የልህቀት ማዕከልነት ሰርተፍኬት አግኝቷል።

የኢትዮጵያ 🇪🇹 አየር መንገድ ይህንን ሰርተፍኬት በማግኘት ከአፍሪካ ቀዳሚው አየር መንገድ ነው፡፡

#የኢትዮጵያአየርመንገድ

@tikvahethiopia
#Update

ወደ ባህሬን ተቋርጦ የነበረው በረራ ከግንቦት 24 ጀምሮ ይጀምራል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደባህሬን አቋርጦ የነበረውን በረራ በሳምንት 3 ጊዜ ከግንቦት 24 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ የሚጀምር መሆኑን ገልጿል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ፦ ከ19 ወራት በኃላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመንገደኞች አውሮፕላን መንገደኞችን ጭኖ መቐለ አሉላ አባ ነጋ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ሲያርፍ የነበረው የመንገደኞች እና የቤተሰቦች ስሜት። #Peace #ETHIOPIA Photo Credit : Tigrai Television @tikvahethiopia
#Update

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአርብ ታህሳስ 21 ቀን  2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ መቐለ የሚያደርገውን መደበኛ በረራ በቀን  ወደ #ሁለት ከፍ ማድረጉን አስታውቋል።

በተከታታይም የመንገደኛ ፍላጎት ቁጥርን ከግምት ውስጥ በማስገባት በቀን የሚያደርገውን የበረራ ምልልስ እንደሚጨምር ገልጿል።

አየር መንገዱ ደንበኞቹ ባሉበት ቦታ ላይ ሆነው በድረገፅ እና የተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያ ተጠቅመው ምዝገባ ማድረግና ትኬት መቁረጥ የሚችሉ መሆኑን አሳውቋል።

www.ethiopianairlines.com 
bit.ly/ET-android-app
bit.ly/ET-iOS-App

#የኢትዮጵያአየርመንገድ

@tikvahethiopia
#ሽረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሰኞ ታህሳስ 24 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሽረ ከተማ በቀን አንድ በረራ ማድረግ እንደሚጀምር ዛሬ ገልጿል።

አየር መንገዱ ፤ ወደ መቐለ የሚያደርገውን መደበኛ በረራ በቀን ወደ ሶስት ከፍ የሚያደርግ መሆኑንም አሳውቋል።

በተከታታይም የመንገደኛ ፍላጎት ቁጥርን ከግምት ውስጥ በማስገባት በቀን የሚያደርገውን የበረራ ምልልስ ብዛት እንደሚጨምርም ገልጿል።

አየር መንገዱ ደንበኞቹ ባሉበት ቦታ ሆነው ባድረ ገፀ እና የተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያ ተጠቅመው ምዝገባ ማድረግና ትኬት መቁረጥ ይችላሉ ተብሏል።

www.ethiopianairlines.com
bit.ly/ET-android-app
bit.ly/ET-iOS-App

#የኢትዮጵያአየርመንገድ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#China ቻይና ከ3 ዓመታት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ድንበሯን #ለጎብኚዎች ከፍት አድርጋለች። ቻይና በመጋቢት 2020 ዓ/ም የኮቪድ  19 ወረርሽኝን ተከትሎ ነበር የጉዞ እግድ የጣለችው። ከአሁን በኃላ ገቢ መንገደኞች ማቆያ ስፍራ መቆየት ሳያስፈልጋቸው በቀጥታ መግባት ይችላሉ። ይሁንና ገቢ መንገደኞች #በ48_ሰዓታት ውስጥ የወሰዱትን የክትባት ማስረጃ ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው ቢቢሲ ፅፏል። @tikvahethiopia
#Ethiopia 🛫 #China 

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ #ቻይና ሳምንታዊ የበረራ ምልልሱን ከፍ ሊያደርግ ነው።

በቻይና መንግስት ተጥለው የነበሩ የኮቪድ-19 ክልከላዎች መነሳታቸውን ይታወሳል።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከመጪው የካቲት ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ ቻይና ወደሚገኙ መዳረሻዎቹ የሚያደርገውን ሳምንታዊ የበረራ ምልልስ ከፍ በማድረግ አገልግሎት መስጠት የሚጀምር መሆኑን አየር መንገዱ ዛሬ አሳውቋል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ

@tikvahethiopia
#ጥንቃቄ

1. አጭበርባሪዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ የእቃ ጭነት አገልግሎት (ካርጎ) በኩል ለተለያዩ ግለሰቦች ዕቃ እንደተላከላቸው አስመስሎ በመደወል እና ሐሰተኛ የእቃ ጭነት መለያ ቁጥር Air Waybill (AWB) በመጠቀም የተላከውን ዕቃ ለመቀበል የሚከፈል በሚል ክፍያ በመጠየቅ የማጭበርበርና የማታለል ስራ እየሰሩ ስለሆነ ጥንቃቄ ይደረግ።

2. አጭበርባሪዎች #ስራ_ፈላጊዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመቀጠር ለምዝገባ እና ለተለያዩ ወጪዎች በሚል ገንዘብ በማስከፈል የማታለል ተግባር ላይ በመሰማራታቸው አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል።

3. የካናዳ መንግስት የስራ እና የትምህርት እድል እንዳወጣ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ሰው እንደወከለ እንዲሁም መመዝገብ ለሚፈልጉም ሁሉ ክፍያ የሚፈፅሙበት የባንክ አካውንትም አንዳሳወቀ በማስመሰል ደብዳቤ በማዘጋጀት ሰዎችን የማታለል ተግባር ላይ አጭበርባሪዎች በመሰማራታቸው ተገቢው ጥንቃቄ ይደረግ።

እንድታውቁት ፦

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዕቃ ለተላከላቸው ደንበኞቹ ዕቃቸው መድረሱን እና ወደ ድርጅቱ በመምጣት አስፈላጊ ሂደቶችን እንዲያስጀምሩ ከማሳወቅ ውጪ ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ እንዲከፍሉ በስልክ አይጠይቅም።

ለስራ ቅጥር በሚል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ አይጠይቅም ፤ ከማንኛውም አይነት ኤጀንት ጋር አብሮ አይሰራም ፤ ለስራም ሆነ ለትምህርት ወደ የትኛውም ሀገር ሰዎችን የመላክ ስራ ላይ አልተሰማራም።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ

@tikvahethiopia
#EthiopianAirlines🇪🇹

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለ7ኛ ጊዜ የአፍሪካ ምርጡ አየር መንገድ በመባል ክብርን ተቀዳጀ።

በአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ' የአቪዬሽን ኦስካር ' ተብሎ በሚጠራው የስካይትራክስ መድረክ ነው ይህን ክብር የተቀዳጀው።

ከዚህ በተጨማሪ ፦

🏆 የአፍሪካ ምርጥ የቢዝነስ ክፍል አየር መንገድ ለ6ኛ ተከታታይ ዓመት

🏆 የአፍሪካ ምርጥ የኢኮኖሚ ክፍል አየር መንገድ ለ6ኛ ተከታታይ ዓመት፣

🏆 በአፍሪካ የኢኮኖሚ ክፍል ምርጥ ምግብ አገልግሎት ሰጪ አየር መንገድ በመባል ተደራራቢ ድልን ተጎናጽፏል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ

@tikvahethiopia
#አቶለማበቀለ👏

አቶ ለማ በቀለ አለሙ በኢትዮጵያ አየር መንገድ በሴኪዩሪቲ ክፍል ውስጥ ነው የሚሰሩት።

በኢትዮጵያዊ ጨዋነትና ሲቀጠሩ በገቡት ቃል መሰረት አየር መንገዱ የሚመራበትን መርህና ሥነ ምግባር እንዲሁም ሙያዊ ታማኝነታቸውን በብቃት በመወጣት ማስመስከራቸውን አየር መንገዱ ገልጿል።

አቶ ለማ በሥራ ገበታቸው ላይ በነበሩበት ወቅት አንድ መንገደኛ ረስተዉ የሄዱትን የእጅ ቦርሳ ውስጡ ከነበረው 71 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ጋር ምንም ሳያጎድሉ በሙሉ ለሚመለከተው የአየር መንገድ ቢሮ ያስረከቡ ሲሆን፤ አየር መንገዱም አስፈላጊውን ማጣራት ካደረገ በኋላ ንብረቱ ለባለቤቱ እንዲመለስ ተደርጓል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM