TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከዓለም ዙሪያ ፦

#ካናዳ ፦ የካናዳው ጠ/ሚ ጀስቲን ትሩዶ አነስተኛ የእጅ ሽጉጥ መግዛትም ሆነ መታጠቅ እንዲከለከል ጠይቀዋል። የትሩዶ መንግሥት በጠቅላላው የእጅ ሽጉጥ መግዛት ሆነ ቤት ማስቀመጥ በሕግ እንዲያስቀጣ ረቂቅ እያወጣ ነው። ረቂቁ እንደሚለው ካናዳዊያን የእጅ ሽጉጦቻቸውን ባይነጠቁም ከዚህ በኋላ አዲስ መግዛት ግን አይችሉም። ትሩዶ ይህን ሐሳብ ያፈለቁት በአሜሪካዋ ቴክሳስ ግዛት አንድ አፍላ ታጣቂ 19 ሕፃናትን ተኩሶ ከገደለ በኋላ ነው።

➡️ #እስራኤል #UAEእስራኤል እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ የነፃ ንግድ ስምምነት ተፈራርመዋል ፤ ይህ እስራኤል ከአረብ ሀገር ጋር ያደረገችው የመጀመሪው ትልቅ ስምምነት ነው።

➡️ #ሴኔጋል ፦ የሴኔጋል ፖሊስ በአንድ ሆስፒታል ውስጥ በደረሰው እና የ11 ህጻናት ህይወት ከቀጠፈው የእሳት አደጋ ጋር በተያያዘ ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተሰምቷል።

➡️ #ሩስያ ፦ በያዝነው ዓመት 70ኛ ዓመታቸውን የሚደፍኑት የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጤና እክል ምናልባትም በካንሰር ህመም እየተሰቃዩ ሳይሆን አይቀርም የሚሉ ያልተረጋገጡ የመገናኛ ብዙኃን ሪፖርቶች እየወጡ ናቸው። የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ግን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ታመዋል መባሉን ሀሰት ሲሉ አስተባበሉ። ላቭሮቭ ፕሬዚዳንት ፑቲን በየቀኑ በአደባባይ እንደሚታዩ እና እንደማኛውም ጤነኛ ሰው የህመም ምልክት አያታይባቸውም ብለዋል።

➡️ #ሶማሊያ ፦ የሶማሊያ ባይዶዋ ከተማ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድን ለመቀበል በዝግጅት ላይ ነች። ከተማዋ ፕሬዝዳንቱ ፈርማጆን አሸንፈው ዳግም የፕሬዜዳንትነት መንበሩን ከተረከቡ በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚጎበኟት ከተማ ትሆናለች።

#ቢቢሲ #ቲአርቲ #ሲጂቲኤን #SNTV

@tikvahethiopia
#እስራኤል

ኔታኒያሁ አፍሪካዊያን ስደተኞችን ከእስራኤል ለማስወጣት ለሚያዝ እቅድ ፍቃድ መስጠታቸው ተነገረ።

በትላንትናው ዕለት በቴል አቪቭ ጎዳናዎች ላይ በኤርትራዊያን ስደተኞች መካከል የተፈጠረውን አስከፊ ግጭት ተፈጥሮ ነበር።

ይህን ተከትሎ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ ደም በተቃባው ግጭት ላይ የተሳተፉት ስደተኞች በሙሉ በአስቸኳይ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ እንደሚፈልጉ አስታውቀዋል።

ጠ/ሚኒስትሩ አክለውም ሁሉም #አፍሪካዊያን ስደተኞች ከእስራኤል እንዲወጡ ለሚያዝ እቅድ ፍቃድ መስጠታቸውንም ገልጸዋል።

ትላንት ቅዳሜ የፕሬዘዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን አስተዳደርን በሚቃወሙ እና በሚደግፉ ኤርትራዊያን መካከል ግጭት ተነስቷል።

ተቃውሞውና ግጭቱ በእስራኤል ኤርትራ ኤምባሲ ፊት ለፊት ነው የተካሄደው። የእስራኤል የአደጋ አገልግሎት ተቋም 114 ሰዎች በግጭቱ ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታውቋል።

የእስራኤል ፖሊሶች የግጭቱን ተሳታፊዎች ለመበተን የፕላስቲክ ቦምቦችን የተጠቀሙ ሲሆን ተቃዋሚዎቹ በፖሊሶቹ ላይ ድንጋይ ወርውረዋል።

አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ፖሊስ ተቃዋሚዎቹ ላይ እሳት መርጨቱን የዘገበ ሲሆን በአጸፋው 27 ፖሊሶች ጉዳት ደርሶባቸዋል ሲል አስታውቋል።

በተያያዘ ሮይተርስ እጃቸው እና ጭንቅላታቸው ላይ ጉዳት የደረሰባቸው ግለሰቦች በህጻናት መጫወቻ ሜዳዎች ሲደበቁ መመልከቱን ዘግቧል።

በእስራኤል 20,000 ኤርትራዊያን ጥገኝነት ጠያቂዎች የሚገኙ ሲሆን አብዛኞቹም በህገወጥ መንገድ በግብጽ አድርገው የመጡ ናቸው።

#ቪኦኤ #ኤኤፍፒ #ሮይተርስ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
የእስራኤልና ፍልስጤሙ ሃማስ ጦርነት በቀጣይ ምን ይዞ ይመጣ ይሆን ?

ዋና ነጥቦች ፦

▪️ሃማስ ፤ " ወራሪ " ናት በሚላት #እስራኤል ላይ  ወታደራዊ ኦፕሬሽን ማካሄድ መጀመሩንይህ ኦፕሬሽንም #ፍልስጤማውያን ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ለደረሰባቸው ግፍ ሁሉ ምላሽ እንደሆነ ገልጿል።

▪️ እስራኤል ፤ " አሸባሪ " የምትለው የሃማስ ቡድን ጥቃት መክፈቱ ከባድ ስህተት መሆኑን በመግለፅ ለእያንዳንዱ ድርጊቱ የከፋ ዋጋ እንደሚከፍልበት ፤ ለሚመጣው ነገር  ሁሉ ኃላፊነቱን እንደሚወስድ ገልጻለች። ሃማስ ላይም መጠነ ሰፊ የአፀፋ እርምጃ ጀምራለች።

▪️እስካሁን ከእስራኤል ከ700 በላይ ከፍልስጤም ከ400 በላይ ሰዎች አልቀዋል።

በእስራኤል እና ሃማስ ጦርነት ሀገራት እና መሪዎች አቋማቸውን እያንፀባረቁ ናቸው።

አንዳንዶቹ በግልፅ ሃማስን " የሽብር ቡድን " እንደሆነ ገልፀው ጥቃቱን ሲያወግዙ አንዳንዶቹ ደግሞ በሁለቱም በኩል ግጭት ቆመ በእርጋታ ነገሮች እንዲፈቱ እየጠየቁ ነው።

እስራኤል አጋሮቿ ሁሉ የተከፈተባትን ጥቃት በግልፅ እንዲያወግዙ ትሻለች።

በወታደራዊና ኢኮኖሚ አቅማቸው ጠንካራ የሆነ የዓለም ሀገራት ምን አቋም ነው የያዙት ?

🇺🇸አሜሪካ - የእስራኤል ወዳጇ #አሜሪካ የ ' ሃማስን ' ጥቃት የአሸባሪዎች ጥቃት ነው በማለት በግልፅ ጥቃቱን አውግዛ ለእስራኤል ሁሉን አቀፍ ድጋፍ አደርጋለሁ ብላለች። ወታደራዊ ድጋፍም ልካለች።

🇫🇷ፈረንሳይ - የሃማስን ጥቃት " የአሸባሪዎች ጥቃት " ስትል ገልጻ ከእስራኤል ጎን እንዳሆነች ገልጻለች።

🇩🇪ጀርመን -ጥቃቱን አውግዛ ከእስራኤል ጎን መሆኗን ገልጻለች። ሃማስንም አሸባሪ ስትል ጠርታለች።

🇮🇳ሕንድ-እስራኤል የተፈፀመባት ጥቃት የአሸባሪዎች ጥቃት ነው ብላ ከእስራኤል ጎን መሆኗን ገልጻለች።

🇬🇧ዩናይትድ ኪንግደም - በእስራኤል ላይ " የሽብር " ጥቃት መፈፀሙን ገልጻ ሀገሪቱ እራሷን የመከላከል መብት አላት ብላለች። ከእስራኤል ጎን እንደሆነችም ገልጻለች።

_

🇮🇷ኢራን - " የፍልስጤም ህዝብ #ራሱን_የመከላከል መብት አለው " ብላ የሃማስን ጥቃት በግልፅ " አኩሪ ተግባር " ስትል አወድሳለች።  " ፍልስጤም እና እየሩሳሌም " ነፃ እስኪወጡ ከፍልሥጤም ተዋጊዎች ጎን እንቆማለን ብላለች።
_

🇨🇳ቻይና- ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት እንዲረጋጉ ፤ ራሳቸውን እንዲቆጣጠሩ እና ጦርነቱን በአስቸኳይ እንዲያቆሙ እንዲሁም ሲቪሎች እንዲጠበቁ ፤ የሁኔታውን እንዳይባባስም እንዲሰሩ አሳስባለች።

ቤጂንግ የሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ የቻይና አቋምን በተመለከተ እስራኤል ሃማስ ላደረሰው ጥቃት ከቻይና ጠንካራ ውግዘት ጠብቃ ነበር ብሏል።

ቻይና የሃማስ ታጣቂ ኃይልን እንደ አሸባሪ ድርጅት ሳይሆን እንደተቃዋሚ ኃይል ነው የምታየው።

🇸🇦 ሳዑዲ አረቢያ - ሀገሪቱ በቅርቡ ከእስራኤል ጋር ያላትን ግንኙነት ለማደስ እየተንቀሳቀሰች ሲሆን አሁን የተቀሰቀሰው ጦርነት በአስቸኳይ እንዲቆም ጥሪ አቅርባለች። ሁለቱም ወገኖች ግጭት እንዲያቆሙና ሲቪሎችም እንዲጠበቁ አሳስባለች።

🇦🇪የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ (UAE) - ያለው ሁኔታ እጅግ እንዳሳሰባት በመግለፅ ግጭት እንዲቆም እና ሲቪሎች እንዲጠበቁ ስትል ጥሪ አቅርባለች።

🇹🇷ቱርክ - በእስራኤልና ፍልስጤም ሃይሎች መካከል የሚካሄደውን ጦርነት ለማረጋጋት ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንደምታደርግ አቋሟን ገልጻለች። ለሁለቱ ሀገራት መፍትሄ ቀጣናዊ ሰላም ማስፈን ብቸኛ መንገድ ነው ብላለች። አሁን ላይ ያለው ከፍተኛ ውጥረት እንዲረግብ እንደምትሰራ ነው የገለፀችው።

🇷🇺 ሩስያ - ሩስያ በአቸኳይ #ተኩስ_እንዲቆም ጥሪ አቅርባለች።

_

አፍሪካውያን ምን አሉ ?

- የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር የሆኑት ሙሣ ፋኪ ማሃማት " የእሥራዔል-ፍልስጥዔም ቋሚ ውጥረት ዋናው ምክንያት የፍልስጥዔም ህዝብ መሠረታዊ መብቶቹን፣ በተለይም ነፃና ሉዓላዊ መንግሥት መነፈጉ ነው " ብለዋል። ሁለቱ ኃይሎች ግጭት አቁመው ወደ ድርድር ጠረጴዛ ይቅርቡ ብለዋል።


- የዩጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቨኒ " በእሥራዔል እና በፍልስጤም መካከል እንዳዲስ ግጭት መቀስቀሱ የሚያሳዝን ነገር ነው። ለምን ሁለቱም ወገኖች የሁለት መንግስት መፍትሄን ተግባራዊ አያደርጉም? በተለይ ደግሞ ሰላማዊ ዜጎችን እና ተዋጊ ያልሆኑ አካላት በታጣቂዎች ዒላማ መደረጋቸው መወገዝ አለበት " ብለዋል።

- #ኬንያ በፕሬዜዳንቷ በኩል ባወጣችው መግለጫ እስራኤል ላይ የተፈፀመው የሽብር ጥቃት መሆኑን በመግለፅ ከእስራኤል ጎን እንደሆነች ገልጻለች።   በተጨማሪ ግጭቱ እንዲበርድ እና እስራኤልም ፍልስጤምም ከወታደራዊ እንቅስቃሴ እንዲቆጠቡ ብላለች።

የUN ፀጥታ ም/ቤት ስብሰባ በምን ተጠናቀቀ ?

ትላንትና ምሽት የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት በእስራኤል - ጋዛ ጦርነት በዝግ አስቸኳይ ስብሰባ ቢቀመጥም አባል ሀገራቱ መስማማት ስላልቻሉ የጋራ መግለጫቸውን ማውጣት አልቻሉም።

አሜሪካ 15ቱ የፀጥታው ምክር ቤት አባላት #ሃማስን አጥብቀው እንዲያወግዙ መጠየቋ ተሰምቷል።

የአሜሪካው ከፍተኛ ዲፕሎማት የሆኑት ሮበርት ዉድ ፤ " የሃማስን ጥቃት ያወገዙ ብዙ አገሮች አሉ። ሁሉም እንዳልሆኑ ግልፅ ነው " ያሉ ሲሆን " እኔ ምንም ሳልናገር ከመካከላቸው አንዱን ማወቅ ትችላላችሁ " ሲሉ ሩስያ ጥቃቱን ካላወገዙት ውስጥ እንደሆነች ተናግረዋል።

መረጃዎቹ ከዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን የተሰባሰቡ ናቸው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ኤርዶጋን ምን አሉ ? የቱርክ ፕሬዝዳንት ሪሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን በእስራኤል እና ፍልስጤም ግጭት ዙሪያ ይህን ብለዋል ፦ - በሲቪሎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ወይም በሲቪል አካባቢዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ትክክል አይደለም፤ አንቀበለውም። - በእስራኤል ግዛት በሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚደርሰውን ግድያ እንቃወማለን። - በጋዛ ውስጥ ንጹሃን  ያለየ ' #ጭፍጨፋ ' በፍጹም አንቀበልም። - አሳፋሪ ዘዴዎችን…
#እስራኤል #ፍልስጤም

ዛሬ አንድ ሳምንቱን የያዘውና ባለፉት ዓመታት ውስጥ ታይቶ አይታወቅም የተባለው እጅግ ደም አፋሳሹ የእስራኤል እና የፍልስጤሙ ሃማስ ጦርነት ቀጥሏል።

አጫጭር መረጃዎች ፦

- እስራኤል እየወሰደችው ባለው ጥቃት የሞቱ ፍልስጤናውያን ቁጥር 1,900 ደርሰዋል። ከሞቱት ውስጥ እጅግ በርከታ ህፃናት ይገኙበታል ተብሏል። 7,696 ሰዎች ደግሞ ተጎድተዋል።

- ሃማስ በሚፈፅመው ጥቃት በእስራኤል በኩል የሞቱ ሰዎች 1400 የደረሱ ሲሆን 3,418 ሰዎች ተጎድተዋል።

- በዌስት ባንክ ውስጥ 52 ሰዎች ሲገደሉ፣ 700 ተጎድተዋል።

- እስራኤል " ሃማስን እስከወዲያኛው አጠፋዋለሁ ፤ ላደረገው ድርጊትም ዋጋውን አስከፍለዋለው " እያለች ሲሆን አሁን ላይ እየወሰደች ያለው እርምጃ ገና መጀማሪያው እንዳሆነ ገልጻለች።

- እስራኤል በሰሜናዊ ጋዛ ያሉ ሁሉም ሲቪሎች በሰዓታት ውስጥ አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ አስጠንቅቃለች። በሰሜናዊ ጋዛ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚገኙ ሲሆን ሀገራት እና ተቋማት እስራኤል ውሳኔዋን እንድታጥፍ እየጠየቁ ናቸው። እንደ ተመድ መረጃ በአስር ሺዎች አካባቢውን ለቀው ወጥተዋል።

- በጋዛ ላይ የነዳጅ፣ የምግብ፣ የውሃ እገዳው አሁንም እንደቀጠለ ነው።

- ሐማስ እስራኤል ላይ አሁንም የሮኬቶች ጥቃት መፈፀሙን ቀጥሏል።

- የሊባኖሱ ታጣቂ ቡድን ሄዝቦላህ የፍልስጤሙን " ሃማስ " በመደገፍ እንደሚሰለፍ አስታውቋል። ቡድኑ ጊዜው ሲደርስ ጦርነቱን ከሃማስ ጎን ሆኖ ለመሳተፍ ሙሉ ለሙሉ ዝግጁ እንደሆነ ገልጿል። ባለፉት ቀናት በሊባኖስ በኩል አንዳንድ የግጭት ምልክቶች የታዩ ሲሆን እስራኤል ድንበሯን ጥሰው ሊገቡ ነበሩ ያለቻቸውን ሰዎች በድሮን መታ መግደሏ ተነግሯል።

- ሐማስ አግቶ ከወሰዳቸው ሰዎች ውስጥ 13 እስራኤላውያንን እና የውጭ አገራት ዜጎች እስራኤል በጋዛ እያደረገችው ባለችው የአየር ጥቃቶች መገደላቸው አሳውቋል።

- የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ወደ ጦርነቱ ቀጠና ሄደው ከእስራኤል ጠ/ሚ እስራኤል ውስጥ፣ ከፍልስጤሙ ፕሬዜዳንት ሞሀሙድ አባስ ጋር ዮርዳኖስ ውስጥ ተገናኝተው መከረዋል። በኃላም ወደ  አጋርናታችንን እናሳያለን ብለው ትላንት እስራኤልን ጎብኝተው ነበር። በኃላም ወደ ሳዑዲ አረቢያ አቅንተው ከሀገሪቱ አመራሮች ጋር ስለጦርነቱ መክረዋል።

- ጦርነቱ እንዲቆም እና መሄጃ ለጠፋባቸው ፍልስጤማውያን ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲደርስ በተለያዩ ወገኖች ጥሪዎች እየቀረቡ ይገኛሉ።

More  @BirlikEthiopia

https://publielectoral.lat/+LM-bJ8NzZMcxMjA8
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ፍልስጤም #እስራኤል

በጋዛ በሚገኝ ሆስፒታል ላይ በተፈፀመ ጥቃት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተገደሉ።

ሃማስ ጥቃቱን እስራኤል ነው የፈፀመችው ብሏል።

የእስራኤል መከላከያ ደግሞ " ኢስላሚክ ጂሃድ " የተባለው ቡድን እስራኤል ላይ ያስወነጨፈው ሮኬት ዒላማው ሳይሳካ ቀርቶ የተፈጠረ ነው ብሏል።

ትላንት ጋዛ ውስጥ በሚገኘው "አልአህሊ ባፕቲስት ሆስፒታል " ላይ በደረሰ የአየር ጥቃት በትንሹ 500 ሰዎች መገደላቸውን በጋዛ  የሚገኘው ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል።

ሃማስ ጥቃቱን እስራኤል ነው የፈፀመችው ብሏል። ጥቃቱን " የጦር ወንጀል ነው" ሲል ገልጾ " ሆስፒታሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ የታመሙ እና የቆሰሉ ሰዎች ነበሩበት ብሏል።

የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት ፤ በጋዛ የሚገኘው ሆስፒታል የተመታው ባያልተሳካ የ " እስላሚክ ጂሃድ " ቡድን ሮኬት ነው ብሏል።

ያልተሳካ ሮኬት ያስወነጨፈው ይኸው ቡድን ለሆስፒታሉ መመታት ተጠያቂ ነው ሲል ገልጿል።

" እኛ ሆስፒታሉ ላይ ጥቃት አልፈፀምንም " ብሏል።

የ " ፍልስጤም እስላሚክ ጂሃድ " ድርጅት የእስራኤል ክስ ሀሰተኛ እና ምንም መሰረት የሌለው የተለመደ ቅጥፈት ነው ብሏል። እስራኤል ከተለመደው ጭፍጨፋ ተጠያቂነት ለማምለጥ በፍልስጤማውያን እና ' ኢስላሚክ ጂሃድ ' ላይ ጣቷን ለመጠቆም የፈጠረችው ሀሰተኛ ፈጠራ ነው ሲል ገልጿል።

" ፍልስጤም እስላሚክ ጂሃድ " እኤአ 1981 የተመሰረተ ሲሆን በጋዛ እና ዌስት ባንክ ውስጥ ይንቀሳቀሳል።

በሌላ በኩል ፤ የፍልስጤም ፕሬዜዳንት ማሃሙድ አባስ በሆስፒታሉ ላይ በተፈፀመው ጥቃት እና በጠፋው የሰው ህይወት ምክንያት የ3 ቀን ሀዘን አውጀዋል።

በሆስፒታል ላይ የተፈፀመውን ጥቃት ሀገራት እና ተቋማት እያወገዙ ይገኛሉ። በተለያዩ ከተሞችም እስራኤልን የሚያወግዙ ሰልፎች እየተደረጉ ይገኛሉ።

ዓለም ለጋዛ ሆስፒታል ለደረሰው ጥቃት ምን ምላሽ ሰጠ ?

እስራኤል የአየር ጥቃቱን ፈፅማለች ብለው የከሰሱና ያወገዙ ፤ በጉዳቱ ሀዘናቸውን የገለፁ ፦

🇪🇬 የግብፅ ፕሬዝዳንት
🇯🇴 የዮርዳኖስ ንጉስ
🇸🇾 የሶሪያ ፕሬዝዳንት
🇨🇺 የኩባ ፕሬዝዳንት
🇮🇶 የኢራቅ መንግስት
🇸🇦 የሳዑዲ አረቢያ መንግስት
🇹🇷የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇻🇪 የቬንዙዌላ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🌍 የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሃላፊ
🇮🇷 የኢራን ፕሬዝዳንት (እስራኤል ብቻ ሳትሆን አሜሪካም ጭምር ከእስራኤል ጋር ሀላፊነት ትወስዳለች ብለዋል)

ጥቃቱን ያወገዙ ነገር ግን ማንንም ያልወቀሱ ፤ ይልቁንም ምርመራ እንዲደረግ የጠየቁ ፦

🇪🇺 የአውሮጳ ዲፕሎማሲ ኃላፊ
🇫🇷 የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት
🇳🇱 የኔዘርላንድስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇪🇸 የስፔን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇬🇧 የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት
🇯🇵 የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
🇺🇸 አሜሪካ ማንም ሳትከስ ነገር ግን ስለ ተፈጠረው ሁኔታ ተጨማሪ መረጃዎችን ሰበስባለሁ ብላለች።

" ማስረጃ አቅርቢ " - ሩስያ

🇷🇺 የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እስራኤል በጥቃቱ ላይ የለሁበትም ካለች የሳተላይ ምስሎችን በማስረጃነት ታቅርብ ብሏል።

እኤአ ጥቅምት 7 ጦርነት ከተቀሰቀሰ በኋላ እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ ባደረሰችው ጥቃት የተገደሉ ሰዎች ከ3,200 በልጠዋል።

በእስራኤል ውስጥ በሃማስ ጥቃት የተገደሉ ከ1,400 በላይ ሰዎች ሆነዋል።

More 👉 @Birlikethiopia