TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ኦነግ⬆️

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር /ኦነግ/ አመራሮች መስከረም 5/2011 አዲስ አበባ እንደሚገቡ የኣቀባበል ኣስተባባሪ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡

ለኦነግ አመራሮች ከቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ጀምሮ ኣቀባበል እንደሚደረግላቸው ኣስተባባሪ ኮሚቴው ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ አስታውቋል፡፡

ኮሚቴው እንዳለው በዚያው ዕለት ለኦነግ አመራሮችና ከውጭ ለሚመጣው የኦነግ ሰራዊት #በመስቀል አደባባይ ልዩ ኣቀባበል ይደረግላቸዋል፡፡

በአቀባበል ስነስርኣቱ ላይ የኦሮሞ ህዝብ ከአዲስ አበባና ከአዲስ አበባ ውጭ #በብዛት ይሳተፋል ብሏል ኮሚቴው፡፡

#ኦነግ በቻርተር ጊዜ የተዘጋብኝን #ጉላሌ ያለውን ቢሮዬን ኣድሼ መቀመጫዬን አዲስ አበባ ኣደርጋለሁ ብሏል፡፡

ከሌሎች የኦሮሞ ፖሊትካ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት እንዳለው ገልፆ፤ ከኦሮሞ ፌዴራልስት ኮንግረስ ጋር #ጥምረት ለመፍጠር ውይይት ላይ ነኝ ብሏል፡፡

©OMN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰላማዊ ሰልፍ አልተጠራም‼️

በአዲስ አበባ ከተማ እሁድ የካቲት 17/2011 ዓ/ም #በመስቀል_አደባባይ ሠላማዊ ሰልፍ ተጠርቷል በሚል በተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች የተላለፈው ዘገባ ሀሰተኛ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በነገው ዕለት ምንም ዓይነት የሠላማዊ ሰልፍ ሆነ ስብሰባ እናድርግ የሚል #ጥያቄ ያልቀረበለት መሆኑን ለኮሚሽኑ የገለፀ ሲሆን ሰልፉ በከተማ አስተዳደሩ ይሁን በፖሊስ ኮሚሽኑ እውቅና የሌለው ነው።
በመሆኑም #ሰልፍ_እንወጣለን በሚል በህብረተሰቡ ላይ የፀጥታ ችግር ለመፍጠር የሚፈልጉ አካላት ከተግባራቸው እንዲታቀቡ ኮሚሽኑ #በጥብቅ አሳስቧል።

ይህን ተላልፎ በሚገኙ አካላት ላይም የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል አስፈላጊውን ህጋዊ #እርምጃ የሚወስድ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል ፡፡

ምንጭ፦ ኢ.ፕ.ድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የምክትል ከንቲባው ምስጋና~ለአዲስ አበቤዎች!

ክብረትና ጤና ይስጥልኝ፦

ዛሬ #በመስቀል_አደባባይ በነበረን ቆይታ እጅግ ደስ ብሎኛል። የሃሴቴ ምንጭ ለጋራ የጤና ጥበቃ እና የመንፈስ መታደስ የታደምነው አዲስአበቤዎች ቁጥራችን ብዙ ስለነበረ ብቻ አይደለም። በጋራ መቆማችን፣ የነበረን ፍቅርን እና ጨዋታ ነው ይበልጥ ያስደሰተኝ።

ሶስት ወራትን ያስቆጠረው የጋራ ስፖርት እንቅስቃሴያችን ካለምነው በላይ ህያው የሆነ ትሩፋት እያጎናፀፈን፣ ለቀጣዩ ወር ይዞት ለሚመጣው ድንቃድንቅ እያጓጓን መጥቷል።

ወንድም እህቶቼ፣ እርስ በእርስ ለመደጋገፍ እና ለጤናችን #መትጋታችንን እንቀጥል። ለሰርከስ፣ ለጂምናስቲክስ፣ ለማርሻል አርት ትርኢት አቅራቢዎች፣ ለጋራ ስፖርት አሰልጣኞች እነሆ የተለየ ምስጋና። #እንደሁሌውም ለምታኮሩኝ አስደናቂዎቹ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ጤና እና ክብረት ይስጥልኝ።

ኢንጂነር ታከለ ኡማ

@tsegabwolde @tikvahethiopia