TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሰበር ዜና📌ቦሌ መንገድ በሚገኘው የፓርላማ አባላት መኖሪያ አፓርታማ አካባቢ ከሌሊት ጀምሮ #የተኩስ ልውውጥ የነበረ ሲሆን፣ የቦሌ መንገድ ሙሉ በሙሉ ተዘግቶ መቆየቱና የሰው #ሕይወት ማለፉ ተሰምቷል፡፡

ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአምቦ ከተማው እርቅ‼️

የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከዛሬ ጀምሮ #የተኩስ_ማቆም ውሳኔ አሳልፈዋል። ከዚህ በተጨማሪም የኦነግ ሰራዊት በጥቂት ቀናት ውስጥ ካለበት ጫካ ወጥቶ ወደ ካምፕ እንዲገባም ውሳኔ አሳልፈዋል። መንግስት እና ኦነግ ውሳኔዎችን ያሳለፉት የኦሮሞ አባ ገዳዎች ህብረት በዛሬው እለት በአምቦ ከተማ ባዘጋጀው የእርቅ ስነ ስርአት ላይ ነው።

በዛሬው እለት በተዘጋጀው የእርቅ ስነ ስርዓት ላይ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስትና የኦነግ ከፍተኛ አመራሮች፣ አባ ገዳዎች፣ ሀደ ሲቄዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የዩኒቨርሲቲ መምህራን፣ ወጣቶች፣ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች እና የአምቦ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል። በመድረኩ ላይም መንግስት እና ኦነግ በኦሮሞ ባህል መሰረት ኮርማ በሬ በማረድ በይፋ የእርቅ ስነ ስርአት ፈጽመዋል።

ሁለቱም አካላት ከዚህ በኋላ ወደ ደም #መፋሰስ እንደማይገቡ እንዲሁም ያለፈውን ነገር በመተው ስለወደፊቱ ብቻ በጋራ ለመስራት በእርቅ ስነ ስርዓቱ ቃል ገብተዋል። በመድረኩ ላይ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ከስምምነት የደረሱባቸው ዝርዝር የውሳኔ ነጥቦች ይፋ ተደርጓል።

ዝርዝር ስምምነቱንም የቴክኒክ ኮሚቴውን በመወከል የፖለቲካ ተንታኝ እና አክቲቪስት አቶ ጀዋር መሃመድ ያቀረቡ ሲሆን፥ ሁለቱንም አካላት በማነጋገር በዝርዝር ውሳኔው ላይ መደረሱን አስታውቀዋል። በዚሀም መሰረት ከዛሬ ጀምሮ በመንግስት እና በኦሮሞ ነፃነት ግንባር መካከል ጦርነት መቆሙን አስታውቀዋል።

ወደ ግጭት የሚያስገቡ ትንኮሳዎችን ሙሉ በሙሉ መከልከሉን እንዲሁም አንዱ በሌላው ላይ ከዚህ በኋላ መግለጫ ማውጣት ሙሉ በሙሉ መከልከሉንም ገልፀዋል። የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ሰራዊት ካለበት ቦታ በሙሉ ትጥቅ ፈትቶ ወደ ካምፕ እንዲገባ መወሱን እና ይህም ከበቂ ጥበቃ ጋር በክብር አቀባበል ወደ ካምፕ እንዲገቡ እንዲደረግ መወሰኑንም ገልፀዋል።

ሰራዊቱን ወደ ካምፕ የማስገባት ስራም በ20 ቀን ውስጥ መጠናቀቅ እንዳለበት ተወስኗል ያሉት አቶ ጃዋር፥ ከእዚህም ውስጥ 10 ቀናት ዝግጅት የሚደረግበት፤ ቀሪው 10 ቀናት ደግሞ ሰራዊቱ ወደ ካምፕ የሚገባበት ነው ብለዋል። ወደ ካምፕ የማስገባት ሂደቱም በሶስት ደረጃዎች ተከፋፍሎ ይካሄዳል ያሉ ሲሆን፥ በዚህም የመጀመሪያም ወደ ወረዳ ከተሞች እንዲሰባሰቡ፣ በመቀጠል ወደ ተዘጋጀላቸው ካምፕ እንዲገቡ ማድረግ በመጨረሻም የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት አቀባበል ማድረግ መሆኑን አስታውቀዋል።

በዚህ ወቅት ትጥቅ ይዞ መንቀሳቀስ ፈፅሞ የተከለከለ መሆኑን እና ይህን ተላልፎ የተገኘ ማንኛውም አካል ላይ መንግሰት ህግን የማስከበር ስራ እንዲሰራ ተፈቅዶለታል ብለዋል። የኦነግ ሰራዊት ካምፕ ከገባ በኋላም አጠቃላይ ስልጠና እንዲወስዱ ተደርጎ የመንግስት የፀጥታ አካላት መቀላቀል ለሚፈልጉ እንደሚያሟሉት መስፈርት እንዲቀላቀሉ መወሰኑንም አስታውቀዋል።

ከዚህ ውጭ ያሉት ደግሞ እንደየፍላጎታቸው በፈለጉት ዘርፍ ስልጠና ወስደው እንዲሰማሩ ድጋፍ እንደሚደረግም አስታውቀዋል። ወደ ካምፕ የገባው ሰራዊትን አያያዝም የቴክኒክ ኮሚቴው በየጊዜው እየሄደ የሚጎበኝ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ሰራዊት አባላት እስካሁን ላጠፉት ጥፋት ይቀርታ መደረጉንም የቴክኒክ ኮሚቴው ተወካይ አቶ ጀዋር አስታውቀዋል። ኤፍ ቢ ሲ እንደዘገበው ከላይ የተዘረዘሩትን ስምምነቶች ጥሶ የተገኘ ማንኛውም አካል ላጠፋው ጥፋት ተጠያቂ እንደሚደረግም ነው የገለፁት።

የኦሮሞ አባ ገዳዎች ህብረት ያዘጋጀው የእርቀ ሰላም መድረክ ባሳለፍነው ማክሰኞ በአዲስ አበባ የኦሮሞ ባህል ማዕከል መካሄዱ ይታወሳል። በመድረኩ ላይም የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) በመካከላቸው የተፈጠሩ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ተስማምተዋል።

እንዲሁም የኦነግን የታጠቀ ሰራዊት ትጥቅ ለማስፈታት እና ሰራዊቱን ወደ ካምፕ ለማስገባት እንዲሁም ሌሎች ስምምነት ላይ የተደረሱ ጉዳዮችን ለማስፈፀም 71 አባላት ያለው የቴክኒክ ኮሚቴ የተቋቋመ ሲሆን፥ የቴክኒክ ኮሚቴውም ከምሁራን 11፣ ከአባ ገዳዎች 54፣ ከኦዲፒ 3 እንዲሁም ከኦነግ 3 አባላት ያለው ነው።

ምንጭ፦ ኢ.ፕ.ድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰላም🕊የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከዛሬ ጀምሮ #የተኩስ_ማቆም ውሳኔ አሳልፈዋል!

#ሼር #share
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በደቡብ ጎንደር ተጨማሪ መስጊድ ተቃጠለ‼️

በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን በጃራ ገዱ አነስተኛ ከተማ ያለ መስጊድ ባልታወቁ ሰዎች ትላንት ለሊት መቃጠሉን የአካባቢው የእስልምና ጉዳይ ምክር ቤት እና የዞኑ አስተዳደር አስታወቁ። ቃጠሎው #ሆን_ተብሎ ለመደረጉ ጠቋሚ ምልክቶች መገኘታቸውንም ገልጿል።

ቃጠሎው የደረሰበት የጃራ ገዱ ከደቡብ ጎንደር ዞን ዋና ከተማ ደብረ ታቦር 100 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ከተማዋ የምትገኝበት የአንዳ ቤት ወረዳ የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት (መጅሊስ) ዋና ጸሐፊ አቶ #እንድሪስ_ሱፊያን ለጀርመን ራድዮ እንደተናገሩት የትላንቱ ቃጠሎ የደረሰው ከለሊቱ ሰባት ሰዓት ገደማ ነው። በቃጠሎውም “ለአካባቢው ብቸኛ የሆነው መስጊድ ወድሟል” ብለዋል።

“ለሊት ላይ #የተኩስ ድምፅ ሰምተን ወደ ቦታው ሔድን፤ ማትረፍ አልተቻለም። ሁሉም ተያይዞ ነው ያገኘንው። በራፉን ሰብረው ገብተው ነው። ቁልፉ ራሱ የተቆለፈበት አልወጣም። እንዳለ ነው የተዘጋበትን ነቅለው ከውስጥ ያሉ አንዳንድ ቁሳቁሶችን አውጥተው አቃጥለውት ያገኘንው። አብዛኞቻችን ጣራው እና ግድግዳው በእሳት ተበልቶ ነው የደረስንው” ሲሉ ዋና ጸሐፊው የዓይን እማኝነታቸውን ሰጥተዋል።

አደጋው መድረሱን ያረጋገጠው የደቡብ ጎንደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት በበኩሉ መስጊዱ የተቃጠለው “በሩ ተሰብሮ ተከፍቶ ከውስጥ ያሉ መፅሀፍት ሲቃጠሉ ተያይዞ መስጊዱ በመቀጣጠሉ” መሆኑን በፌስ ቡክ ገጹ አስታውቋል። ድርጊቱን የፈጸመው አካል ማንነትን ለማጋለጥ ከአካባቢው ነዋሪ ጋር ዛሬ ስብሰባ መካሄዱንም ገልጿል። እስከ እኩለ ቀን በዘለቀው በዚሁ ስብሰባ የዞን እና የወረዳ ኃላፊዎች ተገኝተዋል ተብሏል።

መስጊዱን በማቃጠል የተጠረጠሩ ግለሰቦች እስካሁን አለመያዛቸውን የሚናገሩት የአካባቢው የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ድርጊቱ “ሆን ተብሎ የተፈጸመ ለመሆኑ አመላካች ናቸው” ያሏቸውን ለጀርመን ድምፅ ራድዮ ዘርዝረዋል። “ከፍርስራሹ ማየት እንደቻልነው መስጊድ ውስጥ ሆን ተብሎ ቁርአኖች ተሰብስበው አንድ ቦታ ነው የተቃጠሉት። ሁለተኛ ደግሞ ቁርአኖች የሚደረደሩበት መደርደሪያዎች ከቃጠሎው የተረፈው ነገር አልተገኘም፤ እንዳለ መውጣቱን ያመለክታል። ሌላኛው ደግሞ የመስጊዱ ምንጣፎች ሌላ ሰዋራ፣ ዘወር ያለ ቦታ ቁጥቋጦ ስር ደብቀውት ከረፈደ በኋላ እርሱንም ለማግኘት ተችሏል” ሲሉ አቶ እንድሪስ አስረድተዋል።

በደቡብ ጎንደር ዞን መስጊድ ሲቃጠል በአንድ ሳምንት ውስጥ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ ነው። የትላንትናው ቃጠሎ የደረሰበት የጃራ ገዶ ቀበሌ ሁለት መስጊዶች ከተቃጠሉበት የእስቴ ወረዳ በ50 ኪሎ ሜትር ገደማ ርቀት ላይ የሚገኝ ነው። በጃራ ገዱ ጊዜያዊ የመስገጃ ቦታ ለመቀለስ እና የተቃጠለውን መስጊድ መልሶ ለመገንባት የአካባቢው ነዋሪዎች በምክክር ላይ መሆናቸውን የአካባቢው የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ለጀርመን ራድዮ ተናግረዋል።

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአዳማ ነዋሪዎች እንዳትረበሹ...

እየሰማችሁት ያለው #የተኩስ ድምፅ በአሉን አስመልክቶ የተዘጋጀው ወታደራዊ ትርኢት አንዱ አካል ስለሆነ በምትሰሙት ተደጋጋሚ የተኩስ ድምፅ እንዳትረበሹ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የወላይታ ሶዶ ውሎ‼️

በደቡብ ክልል በወላይታ ሶዶ ከተማ ዙሪያ ህገወጥ የተባሉ ቤቶች #መፍረሳቸውን ተከትሎ በከተማይቱ ዛሬ ግርግር እንደነበር ነዋሪዎች ተናገሩ። በከተማይቱ #የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበርም የዓይን እማኞቹ ገልጸዋል።

አቶ ዳንኤል ዓለሙ የተባሉ የከተማይቱ ነዋሪ ለጀርመን ራድዮ እንደተናገሩት በከተማይቱ #ግርግር የተቀሰቀሰው ዛሬ እኩለ ቀን አካባቢ ነበር። የግርግሩ መነሻም በተለምዶ “የጨረቃ ቤቶች” ተብለው የሚጠሩ በከተማይቱ ዙሪያ ከተገነቡ መኖሪያ ቤቶች መፍረስ ጋር የተያያዘ እንደሆነም ገልጸዋል። “በጣም ግርግር ነበር። የተወሰነ ጥይት ተኩሰዋል። ሰው ሩጫ ላይ ነበር” ሲሉ የነበረውን ሁኔታ ገልጸዋል።

ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ ሌላ የከተማይቱ ነዋሪም ከቀኑ ስድስት በኋላ ጥይት ይሰማ እንደነበር አረጋግጠዋል። የቤቶችን መፍረስ በመቃወም መንገድ ዘግተው የነበሩ ሰዎችን ለመበተን ፖሊስ አስለቃሽ ጭስ መተኮሱንም የዓይን እማኙ ገልጸዋል። ግርግሩን የፈሩ ሱቆች እና ምግብ ቤቶች ተዘግተው መዋላቸውን የሚናገሩት እኚሁ ነዋሪ ወደ 10 ሰዓት ገደማ ግን ከተማይቱ “ወደ ሰላማዊ ሁኔታ ተመልሳለች” ብለዋል።

በወላይታ ሶዶ ህገወጥ ናቸው የተባሉ ቤቶች እየፈረሱ የሚገኙት ቀድሞ የገጠር ቀበሌዎች የነበሩ ነገር ግን ከአንድ ዓመት ወዲህ በከተማይቱ ክልል ስር በተካተቱ ሶስት አካባቢዎች እንደሆነ ነዋሪዎች ለDW አስረድተዋል። ላሬና፣ ኦፎሳሬ እና ቆንቶ በተባሉት በእነዚህ ቦታዎች የእየፈረሱ ያሉት ቤቶች በመቶዎች የሚቆጠሩ እንደሆኑ ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።

የወላይታ ሶዶ ከተማ ባህል፣ ቱሪዝም እና የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት የኮሚዩኒኬሽን የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ መንግስቱ ቶራ ዛሬ በከተማይቱ የተፈጠረው ግርግር “የህገ ወጥ ግንባታን ለመከላከል እየተደረገ ካለው እንቅስቃሴ ጋር የተያያዘ አይደለም” ሲሉ አስተባብለዋል። “ሰባት ሰዓት አካባቢ ጎማ በመቃጠሉ ሰዉ አመጽ ሊቀሰቀስ ነው በሚል ሰግቶ፣ ፈርቶ ነበር። ግን ምንም ነገር የለም። ተረጋግቷል” ሲሉ ለጀርመን ራድዮ ተናግረዋል።

የከተማይቱ የባህል፣ ቱሪዝም እና የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ዛሬ በፌስ ቡክ ገጹ ባወጣው መግለጫ ካለፈው ከትላንት ጀምሮ የሶዶ ከተማ አስተዳደር እና በዙሪያ ያለው ወረዳ ህገወጥ ግንባታ የመከላከል እና የህግ የበላይነትን የማስከበር ስራ እየሰሩ እንደሚገኙ አስታውቋል። በህገወጥ ግንባታ ተሳታፊ የሆኑ ግለሰቦች “ስራውን ለማስተጓጎልና የከተማውን ጸጥታ ለማወክ” መሞከራቸውንም ጠቁሟል። “መንገድ በመዝጋት፣ ደን የማቃጠል ሙከራ በማድረግ እና ሌሎች ችግሮችን ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸዋል” ያላቸው ግለሰቦችም “#በቁጥጥር ስር ውለዋል” ብሏል።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"የማረጋጋት ስራ እየሰራሁ ነው" - መከላከያ

የሀገር መከላከያ ሰራዊት ግጭት ተከስቶ በነበረባቸው በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር እና በሰሜን ሸዋ ዞኖች መካከል በመግባት የማረጋጋት ስራ እያከናወነ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሚንስቴር የማረጋጋት ስራውን በመስራት ላይ የሚገኝው የአማራ ክልል መንግስት ባቀረበለት ጥሪ መሰረት እንደሆነ ገልጿል፡፡

አሁን ላይ አካባቢዎቹ #እየተረጋጉ ቢመጡም አልፎ አልፎ በመንገድ ዳርቻዎች ላይ #የተኩስ ልውውጦች አሉ ነው የተባለው፡፡ የተኩስ ልውውጡ የሚሰማው በገጠራማ አካባቢዎች መሆኑ ነው የተነገረው፡፡

አካባቢዎቹ ሰፊ እንደመሆናቸው በብቃት ለመቆጣጠር #ተጨማሪ ሀይል ወደ ስፍራዎቹ #እየገባ መሆኑን ሚንስቴሩ ይፋ አድርጓል፡፡

ተዘግተው ያሉ የደሴ፣ ኮምቦልቻ፣ ደብረ ሲናና እና ደብረ በርሃን መንገዶችን የማስከፈት ስራ #እንደሚከናወንም ተጠቁሟል፡፡

ምንጭ-#ፋና
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#BREAKING

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፌዴራል መንግስት ሰብዓዊነትን መሰረት ባደረገና ተጨማሪ ጉዳት በማያስከትል መልኩ #የተኩስ_አቁም_ስምምነት እንዲያደርግ ጥያቄ ማቅረቡን አስታወቀ።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር አብርሃም በላይ እንዳስታወቁት፥ ክረምት እየገባ በመሆኑ የትግራይ ክልል አርሶ አደር ተረጋግቶ የእርሻ ስራውን እንዲያከናውን፣ የሰብዓዊ ድጋፍ ለተረጂዎች ያለምንም ችግር እንዲደርስ ወቅቱን የሚመጥን ፖለቲካዊ መፍትሄ ለመስጠት የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያደርግ ተጠይቋል ብለዋል።

ዶ/ር አብርሃም በላይ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ጥያቄውን ባለፈው ሳምንት በይፋ ማቅረቡን ገልፀዋል።

ይህ ጥያቄ የቀረበው የክልሉን ወቅታዊ ሁኔታን አስመልክቶ ከክልሉ ህዝብ ተወካዮች ፣ ከቢሮ እና ዞኖች አመራር አባላት፣ በተለያየ ቦታ ከሚገኙ የትግራይ ተወላጆች፣ ከትግራይ ምሁራን፣ ከባለሀብቶችና ከሃይማኖት አባቶች ጋር ተከታታይ ምክክር ካደረገ በኋላ ነው ብለዋል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/ENA-06-28-2

#ኢዜአ

@TIKVAHETHIOPIA
#ETHIOPIA

ለሰሜን ኢትዮጵያ ችግር ሰላማዊ የሆነ መፍትሄ ለመፈለግ እና ችግሩን በሰላማዊ ድርድር ለመቋጨት በፌዴራሉ መንግስት የተቋቋመው " የሰላም አማራጭ አብይ ኮሚቴ " ዛሬ መግለጫ ሰጥቶ ነበር።

በመግለጫው ላይ ከተጠቀሱ #ወሳኝ ነጥቦች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል ፦

• ኮሚቴው ባደረገው ውይይት የትግራይ፣ የአፋር፣ የአማራ ክልል አካባቢዎች ነዋሪ የሆኑ ዜጎች በእለት ተእለት ኑሮዋችው ላይ እየገጠማቸው ያለውን ችግር መቀረፍ እንደሚገባ ፤ የሰብዓዊ ድጋፍ አስተማማኝ እና ዘላቂ በሆነ መንገድ ለማድረስ ይቻል ዘንድ ፣ እንዲሁም የመሰረተ ልማት እና የመሰረታዊ አገልግሎቶችን ዳግም ስራ ለማስጀመር አስቻይ የሆነ ሁኔታ በፍጠነት ለመፍጠር ፤ #የተኩስ_አቁም_ስምምነት ላይ በአጭር ጊዜ ላይ መድረስ እንደሚገባ አጽኖት ሰጥቷል።

• ወደ ተኩስ አቁም ስምምነት ሊያደርስ የሚችል እና ለቀጣይ የፖለቲካ ውይይቶች መሰረት የሚጥል የሰላም ምክረ ሃሳብ ላይ ውይይት በማድረግ የምክረ ሃሳብ ሰነድ አጽድቆዋል።

• የሰላም ምክረ ሃሳቡ በተቻለ ፍጥነት ለአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ ወኪል እንዲቀርብ ወስኗል።

• ወደተኩስ አቁም ስምምነት ሲገባ በሚፈጠረው አስቻይ ሁኔታ፣ መሰረታዊ አገልግሎቶችን #በተቻለ_ፍጥነት መልሶ ማቅረብ ይቻል ዘንድ፣ አስፈላጊ ቅደም ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን ገልጿል።

• የአፍሪካ ህብረትም የሰላም ንግግሩ በአስቸኳይ ተጀምሮ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መድረስ ይቻል ዘንድ፣ የሰላም ንግግሩ የሚካሄድበትን ቦታ እና ጊዜ በፍጠነት ወሰኖ ንግግሩ እንዲጀመር፣ ይህን ማድረግ ይቻል ዘንድ ከአፍሪካ ህብረት ጋር በቅርበት እየተሰራ እንደሆነ ገምግሟል።

(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ከቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ፦

(የፀጥታ ጉዳዮች)

ከቀናት ለፊት በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ቤተሰቦቻችን በተለይ በወለጋ አካባቢዎች በፀጥታ ችግር ከፍተኛ ችግር እያጋጠማቸው መሆኑን ፣ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ባሉ ችግሮች ንፁሃንን ሰለባ እየሆኑ እንደሚገኙ ፣ ሚማሩበት ዩኒቨርሲቲ የጠራቸው ተማሪዎች መንገድ በመዘጋቱ በእግር ለመጓዝ እንደተገደዱ መግለፃቸው አይዘነጋም።

በእርግጥ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ላይ ያለው የፀጥታ ችግር ዘላቂ እና አስተማማኝ መፍትሄ ሳያገኝ የበርካታ ንፁሃንን ህይወት እየቀጠፈ እንሆ አመታት አልፈዋል ፤ አሁንም ቀጥሏል ፤ በፀጥታ ችግሩ ሳቢያ ኢኮኖሚው ተጎድቷል፣ ገበሬዎች ማረስ እንዳችሉ ሆነዋል በርካቶች የሰው እጅ ጠባቂ ሊሆኑ ተገደዋል።

ከሰሞኑን ደግሞ የፀጥታ ችግሩ እስከ ትልቋ የነቀምቴ ከተማ ደርሶ ነበር።

ባለፈው እሁድ ዕለት በከተማይቱ መንግስት 'ሸኔ' ሲል በሽብርተኝነት የፈረጀው እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እያለ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን ወደ ከተማይቱ ዘልቆ በመግባት ከመንግስት የፀጥታ ኃይል ጋር #የተኩስ ልልውጥ አድርጎ ነበር።

በዕለቱ የደረሱ ጉዳቶች ስለመኖራቸው (ትክክለኛውን ለመግለፅ ቢያስቸግርም) ፣  ነገር ግን ሁኔታውን የፀጥታ ኃይሉ መቆጣጠር እንደቻለ ከቤተሰቦቻችን ተገልጾልናል።

ይህን ያህል በትልቅ ከተማ ውስጥ የተኩስ ልውውጥ እስኪደረግ የፀጥታና ደህንነት ኃይሉ ምን ይሰራ ነበር የሚለው " ትልቁ ጥያቄያቸው " እንደሆነ ቤተሰቦቻችን ነግረውናል።

የነቀምቴ ከተማ አስተዳደር ለማህበረሰቡ እና ለመላ ለአገልግሎት ሰጪዎች ባሰራጨው አጭር መልዕክት ፤ በቅርቡ ነቀምቴ ከተማ ውስጥ በሸኔ ቡድን የፀጥታ ችግር ተፈጥሮ እንደነበር ገልጾ ችግሩ በፀጥታ ኃይሉ ቅንጅት ፣ በከተማው ህዝብ ተሳትፎ እንዲረጋጋ መድረጉን አመልክቷል።

ነቀምቴ ከተማ አሁን ላይ ሰላም በመሆኗ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ፣ የአገልግሎት ሰጪዎች (የትራንስፖርት ፣ ባንክ ...የመሳሰሉ) ወደ ስራ ተመልሰው አገልግሎት እንዲሰጡ የከተማው አስተዳደር አሳስቧል።

                                 --------

በአ/አ - ሀዋሳ ፈጣን መንገድ ላይ " መቂ " አካባቢ ምንድነው የሆነው ?

ከትናንትና በስቲያ ምሽት 2 ሰአት አከባቢ ከአ/አ ወደ ሃዋሳ በሚወስደው ፈጣን መንገድ ላይ መቂ አከባቢ ሲጓዙ በነበሩ ተሳፋሪዎች ላይ በታጣቂዎች ተኩስ ተከፍቶ የሰዎች ህይወት ስለማለፉ አንድ የቤተሰባችን አባል ገልጿል።

ይህንን ክስተት የገለፀው የሻሸመኔ፤ ቲክቫህ ቤተሰብ አባል ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ " ወንድም እና እህት መሞታቸውን አረጋግጫለሁ " ብሏል።

በወቅቱ ከተሳፋሪዎቹ አንዷ የእሱ #እህት እንደነበረች በመግለፅ በጥቃቱ ሳቢያ የቆሰሉ ሰዎች እንደነበሩ አመልክቷል።

ሟቾቹ የሻሸመኔ ከተማ 04 ቀበሌ ውሃ ልማት አካባቢ ነዋሪዎች እንደሆኑ ጠቁሟል።

የኸው ቤተሰባችን በዚያው ሰአት ከአዲስ አበባ እቃ ጭነው ሲመጡ የነበሩ ተሽከርካሪዎች መቃጠላቸውን እንደሰማ ገልጿል።

እስካሁን በዚህ ጉዳይ ከመንግስት በኩል የተባለ ነገር የለም።
 
                                 --------

በአሶሳ ምንድነው ያለው ?

" አሶሳ ፍፁም ሰላም ነች "

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዋና ከተማ አሶሳ ከተማ ከሀሙስ ከሰአት ጀምሮ ኔትዎርክ፣ ሲስተም ፣ መብራት ጠፍቶ ነበር።

ትላንት ከሰዓት ኔትወርክ / ሲስተም የተመለሰ ሲሆን ይህ መልዕክት እስከተላከበት ሰዓት መብራት የለም።

አንድ የአሶሳ የቤተሰባችን አባል በላከው መልዕክት ፤ " ስለጉዳዩ ከመንግስት በኩል የተነገረ ምክንያት የለም " ያለ ሲሆን " አሶሳ ከተማ ግን ባለፉት 6 ቀናት ከባንኮች መዘጋት በስተቀር  እጅግ ሰላማዊና መደበኛ የስራ እንቅስቃሴዎች አንዳሉ ናቸው። " ብሏል።

በኔትወርክ መጥፋት ምክንያት የተጨነቁ ቤተሰቦችም ሁሉም ነገር ሰላም ስለሆነ ጭንቀት እንዳይገባቸው መልዕክት አስተላልፏል።

ከሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል " ምዕራብ ወለጋ " አካባቢ ካለው የፀጥታ ችግር ጋር በተያያዘ በአሶሳ ኔትዎርክ መቋረጡ ያሳሰባቸው በርካቶች ሲሆኑ አሶሳ ከተማና አካባቢው ላይ ኔትዎርክ ከመቋረጥ በዘለለ / አሁን ላይ ኔትዎርክ ተመልሷል / ሁሉም ነገር #ሰላም ነው።

በሌላ በኩል፦ በአሶሳ ዞን #ባንባሲ ወረዳ ከወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ጋር በተያያዘ (ወረዳው የስጋት ቀጠና በመሆኑ ምክንያት) ከቀናት በፊት የታወጀው የሰዓት እላፊ ተግባራዊ እየሆነ ነው።

ለማስታወስ ያህል ፦

- እግረኞች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12፡00 ሰዓት ምንም እንቅስቃሴ ማድረግ አይችሉም።

- ሞተር ሳይክሎችና 3 እግር ተሽከርካሪዎች ከምሽቱ 1:00 - ንጋቱ 12:00 ሰዓት ምንም እንቅስቃሴ ማድረግ አይችሉም።

- ማንኛውም የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሻይ ቡና፣ ምግብ ፣ ሪስቶራንት፣ መጠጥ ቤቶች እና ወ.ዘ.ተ ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ማድረግ አይችሉም።

በተጨማሪ ፦ ማንኛውም የጸጥታ አካል ከተመደበው #መደበኛ_ሠራዊት_ውጪ የተጣለውን የሰዓት እላፊ ገደብ አልፎ ሲንቀሳቀስ ከተገኘ በቁጥጥር ስር ይውላል።

@tikvahethiopia