TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update በሻሸመኔ ከተማ ተካሂዶ በነበረው ህዝባዊ የአቀባበል ስነስርዓት ጊዜ #በአሰቃቂ ሁኔታ የሰው ህይወት አጥፍተዋል የተባሉ ሁለት ግለሰቦች በእድሜ ልክ እስራት ተቀጡ።

የሻሸመኔ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር #መኮንን_ታደሰ ለሸገር ራድዮ እንደተናገሩት በሻሸመኔ በነበረው ህዝባዊ የአቀባበል ስነ ስርዓት ጊዜ በአሰቃቂ ሁኔታ የአንድ ሰው ህይወት አጥፍተዋል የተባሉ ሁለት ግለሰቦች ጉዳያቸው በፍርድ ቤት ሲታይ ቆይቶ ሰሞኑን እያንዳንዳቸው በእድሜ ልክ እስራት እንዲቀጡ ተወስኖባቸዋል ብለዋል። ኮማንደር መኮንን ውሳኔውን ያሳለፈው የምዕራብ አርሲ ከፍተኛው ፍርድ ቤት እንደሆነም ተናግረዋል።

በሻሸመኔ ከነበረው ህዝባዊ የአቀባበል ስነ ስርዓት ጋር በተገናኘ የሰው ህይወት አጥፍተዋል ንብረትም አውድመዋል ተብለው የተጠረጠሩ 16 ሰዎች ተይዘው እንደነበር በምስክር #መጥፋትም አስሩ ተለቀው ስድስቱ ተጠርጣሪዎች እንደቀሩ ሸገር በዘገባው አስታውሷል።

Via Shger FM 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia