TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኬንያ(ናይሮቢ)🛫

ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድና የሶማሊያው ፕሬዚዳንት መሐመድ አብዱላሂ መሐመድ ከኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር #ለመወያየት በአሁኑ ወቅት ወደ #ናይሮቢ ኬንያ አቅንተዋል።

ጠ/ሚር ዶ/ር #ዐቢይ_አሕመድ በሶማሊያና ኬንያ መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት እንደ ምሥራቅ አፍሪካ በይነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ) ሊቀ መንበርነታቸው በቅርበት በመከታተል ወደ #ዕርቅ የሚመጡበትን መላ እያፈላለጉ ነው።

ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ የኬንያው ፕሬዚዳንት ኬንያታና የሶማሊያው አብዱላሂ መሐመድ ወደ ኢትዮጵያ ለይፋዊ ጉብኝት በዘለቁ ወቅት ከሁለቱም ጋር ባደረጉት ምክክር፤ ይህንን የኬንያና የሶማሊያ መሪዎች የፊት ለፊት ውይይት ለማመቻቸት ወስነው ነበር። ይህ የውይይት መድረክም በሁለቱ መካከል ያለውን የተካረረ ውጥረት ያረግባል ተብሎ ይታመናል።

ምንጭ፦ የጠቅላይ ሚር ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር ዜና‼️

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ ቦይንግ 737 አውሮፕላን ዛሬ ጠዋት #ከአዲስ_አበባ ተነስቶ ወደ ኬንያ #ናይሮቢ ሲበር #ተከስክሶ የሰው ህይወት አልፏል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በኬንያ የአህያዎች ቁጥር ከዕለት ዕለት እየተመናመነ ነው። መቀመጫውን #ናይሮቢ ያደረገው የአፍሪካ የእንሰሳት ደህንነት ተሟጋቾች ቡድን እንዳጠናው ከሆነ የአህያ ዝርያ የመጥፋት አደጋ ተጋርጦበታል። ሶስት አመት በፊት በኬንያ አራት የአህያ ቄራዎች መከፈታቸውን ተከትሎ በቀን ብዙ አህዮች ይታረዳሉ። ድርጅቱ እንደሚለው ከሆነ በሥራ ቀናት በሳምንት በትንሹ 410 አህዮች ይታረዳሉ። የአህያዎቹ ቆዳም ወደ ቻይና ይላካል። ድርጅቱ እንደሚለው ኑሯቸውን በአህያ አገልግሎት ላይ የመሠረቱ ማኅበረሰቦች ቄራዎቹ ከተከፈቱ በኋላ ለችግር ተጋርጠዋል። በኬንያ አሁን ያሉት አህዮች ብዛት በድምሩ 2 ሚሊዮን ይጠጋል።

Via #BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Peace የተደራዳሪ ቡድኑ ! የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት #በሰላም_ድርድር እንዲፈታ ገዢው የብልፅግና ፓርቲ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል። በዚህም መሰረት በፌዴራል መንግሥት በኩል የሰላም ተደራዳሪ ቡድን መሰየሙ ተረጋግጧል። የቡድኑ አባላት ፦ 1ኛ. አቶ ደመቀ መኮንን ➡️ ሰብሳቢ 2ኛ. ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቲዎስ ➡️ አባል 3ኛ. አቶ ተመስገን ጥሩነህ ➡️ አባል 4ኛ. አምባሳደር ሀሰን አብዱልቃድር ➡️
#Update

ከጥቂት ሳምንታት በፊት የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በሰላም መቋጫ እንዲያገኝ የፌዴራል መንግስት የሰላም ተደራዳሪ ቡድን መቋቋሙ ይታወሳል።

የተደራዳሪ ቡድን አባላቱም ይፋ መደረጋቸው አይዘነጋም።

አሁን ደግሞ ትግራይ ክልልን እያስተዳደረ የሚገኘው ህወሓት ተደራዳሪ ቡድን ማቋቋሙን ገልጿል።

የህወሓት ቃል አቀባይ ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የዜና ወኪል በሰጡት ቃል ፤ ለድርድር የሚሆን ልዑክ ወደ #ናይሮቢ ለመላክ ዝግጁ እንሆናለን ብለዋል።

በከፍተኛ ሥልጣን ደረጃ የሚገኙ አባላት ያሉት ኮሚቴም ተቋቁሟል ሲሉ አሳውቀዋል።

ተደራዳሪ ሊሆኑ የሚችሉ ግለሰቦች እነማን እንደሆኑ እንዲሁም ቁጥራቸውን በተመለከተ የተባለ ነገር የለም።

ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ መንግስት ከህወሓት ጋር የሚደረገው ምንም አይነት ድርድር ሊመራ የሚችለው በአፍሪካ ኅብረት ብቻ መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን፣ የህወሓት አመራሮች ድርድሩ በኅብረቱ ጥላ ስር ብቻ እንዲሆን እንደማይፈልጉ ገልጸዋል።

" ሁሉንም የድርድር ሂደቶች ለአፍሪካ ኅብረት መስጠቱ ለእኛ በጣም ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው” ያሉት አቶ ጌታቸው፣ ማንኛውም ድርድር በሰላም ጥረት ውስጥ ንቁ ሚና የተጫወቱትን ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታን ማካተት አለበት " ብለዋል።

መረጃው የአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ /ቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia