TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ሀዋሳ⬇️

በሀዋሳ ከተማ የተለያዩ #የጦር_መሳሪያዎች እና #ስለታም ነገሮችን ይዘው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ አምስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ፡፡

በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የአድማ ብተና እና ልዩ ኃይል ዘርፍ ኃላፊ በምክትል ኮሚሽነር ማዕረግ መሳፍንት ሙሉጌታ እንደገለጹት በሀዋሳ ከተማ መስከረም 17 ቀን 2011 ዓ.ም በተለያዩ ቦታዎች በተደረገው #ፍተሻ 3 ስታር #ሽጉጥ የተለየዩ ስለታማ መሳሪያዎችና 834 ሺህ ብር መያዙን ገልፀዋል፡፡

እንደ ኃላፊው ገለጻ የፀጥታ አካሉ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥና የከተማውን ሠላም ለማስጠበቅ በቋሚና ተንቀሳቃሽ ጥበቃ እያደረገ እንደሚገኝና በዚህም አምስት ግለሰቦት የጦር መሳሪያዎችንና ስለታማ ጩቤዎችን ይዘው ሲንቀሳቀሱ በድንገት በተደረገው ፍተሻ በጎድጓዳ፣ ጥቁር ውሃ እና ታቦር ክፍለ ከተማ እንደተያዙ አስረድተው ግለሰቦቹ ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል ሲል የኮሚሽኑ ሕዝብ ግንኙነት ዳይሮክተሬት ዋና ሳጅን ደጀኔ አሰፋ አስረድተዋል።

©የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia