TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የትግራይ ዲያስፖራ ፌስቲቫል!

2ኛው ዓለምቀፍ የትግራይ ዲያስፓራ ፌስተቫል ለመካሄድ የሚያስችል ዝግጅት
#መጠናቀቁን የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አስታውቋል፡፡

ፌስቲቫሉ በተለያዩ የዓለም ሃገራት የሚገኙ የትግራይ ዲያስፓራ ማህበረሰብ በክልሉ ብሎም በሃገራቱ እየተከናወኑ ባሉት የሰላም የዴሞክራሲና የልማት ስራዎች ተሳታፊ ለማድረግ ያለው ነው ተብሏል፡፡

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የከተማ ልማትና ንግድ ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር #አብርሃም_ተከስተ ዝግጅቱን አስመልክቶ በሠጡት መግለጫ ፌስቲቫሉ የትግራይ ዲያስፓራ ስለሃገራቸውና ስለ ክልላቸው ተጨባጭ ሁኔታ ተገንዝበው ለትግራይ ህዝብ ሰላምና ደህንነት በተደራጀ መልኩ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ለማድረግ ነው፡፡

ፌስቲቫሉ ዲያስፓራውን በክልሉ በሚካሄደው የንግድ የኢንቨስትመንትና የኢንዱስትሪ ልማት እንቅስቃሴዎች ተሳታፊ ለማድረግ ነው ያሉት ዶክተር አብርሃም የፐብሊክ ዲኘሎማሲውን በማጠናከር በኢትዮ ኤርትራ የተጀመረውን የሰላም ግንኙነት ተጠናክሮ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ነው፡፡

ዋናው ፌስቲባል ከሃምሌ 24 -ሃምሌ 3ዐ/ 2ዐ11 ዓ.ም ድረስ የሚካሄድ ሲሆን የህዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ /ህወሓት/ የተመሰረተበትን ቀን ምክንያት በማድረግ ከየካቲት 11/2ዐ11 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ስነ-ስርዓቶች እንደሚካሄደ ተገልጿል፡፡

ምንጭ፦ ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia