TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Update የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና⬆️

2ኛው ቀኑን የያዘው የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች #ስልጠና እንደቀጠለ ነው።

በዛሬው ዕለት:-

* ለህዝብ ቅርብ መሆንና በሚረዳው ቋንቅ ማናገር (How to be closer to the people and address them effectively in their setting?)

* ልህቀትን የሚያመጣ የአመራር ክህሎት (Leadership for Excellence)

* ፕሮቶኮል፣ የጊዜ አጠቃቀም እና ተያያዥ ጉዳዮች (Protocol, Etiquette and Time management)

* ውጤታማ የንግግር ክህሎት (Effective Public Speaking) በሚሉ ርዕሶች በአገር ውስጥ እና በውጭ -ባለሙያዎች ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

ስልጠናውና ውይይቱ በዛሬው ዕለት #እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡

ምንጭ፡- ጠ/ሚ ጽ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኦነግ ሰራዊት አባላት‼️

ከ1 ሺህ በላይ የሚሆኑ የኦነግ ሰራዊት አባላት ወደ ተዘጋጀላቸው #ካምፕ ገብተዋል።

የሰራዊት አባላቱ ጦላይን ጨምሮ በኦሮሚያ ክልል በተዘጋጁ የተለያዩ ካምፖች በመግባት #ስልጠና እየወሰዱ ነው።

ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የሰራዊት አባላቱ፥ የተደረገላቸው የሰላም ጥሪና እየታየ ያለው የፖለቲካ ለውጥ ለሃገርና ህዝብ ጥቅም በሰላማዊ መንገድ እንዲታገሉ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል።
በሃይል ትግል ማድረጉም ለህዝቡ ስለማይጠቅም ሰላማዊ የትግል መንገድ መምረጣቸውንም ነው የተናገሩት።

ከዚህ በተቃራኒው የትጥቅ ትግልን አማራጭ በማድረግ በሃይል የሚንቀሳቀስ ቡድን አካሄድ ተቀባይነት እንደሌለውም ገልጸዋል፤ ለውጡን ለማስቀጠል መናበብና መመካከር አስፈላጊ መሆኑን በመጥቀስ።

ከዚህ ባለፈም የበርካቶች ህይወት ያለፈበትን ትግል ማደናቀፍ እንደማይገባ የጠቀሱት አባላቱ፥ የአንድ ሃገር እድገትን ለማረጋገጥ በሰላማዊ መንገድ መታገል አስፈላጊ መሆኑንም አንስተዋል።

በትጥቅ ትግል ላይ ለሚገኙ ሌሎች ጓዶቻቸውም ትጥቃቸውን ፈተው ሰላማዊ ትግሉን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የጦላይ ስልጠና ማዕከል አስተባባሪ ኮሚሽነር ፀሃይ ነጋሽ በበኩላቸው አባላቱ በህገ መንግስቱ፣ በፌደራሊዝሙና በሃገራዊ ለውጡ ዙሪያ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን ገልጸዋል።

ምንጭ፦ ኢ.ፕ.ድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከጅማ ዞን📩

"በጅማ ዞን #የፓስፖርት ጉዳይ አሳሳቢ ነው፤ በተለይ ለወንዶች፤ ፓስፖርት ለማውጣት ስንፈልግ #ስልጠና ውሰዱ ይሉናል ለወንዶች ስልጠና የሚሰጥ አካል ግን የለም። ለሚመለከተው አካል ብንናገርም ምላሽ ሚሰጠን ሰው የለም።" #አለልኝ

መላሽ የሚሰጥ አካል ካለ @tsegabwolde
@tsegabwolde @tikvahethiopia