TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
“ሐይማኖቶች #የሰላም ባለቤቶች ናቸው፡፡ በሀገራችን ሀይማኖት ብቻ ሳይሆኑ የእርስ በርስ የባህል ልውውጥ ማዳበሪያ፣ ችግሮችን #መሻገሪያ ድልድይ ናቸው” የኢትዮጵያ ሐይማኖቶች ጉባኤ ዋና ፀሐፊ መጋቢ #ዘሪሁን_ደጉ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኦነግ/WBO‼️

የ'ኦነግ' የቅበላ ቀነ ገደብ ተጠናቋል!
(*የልዩ ሁነት #አምስት የመጨረሻ ቀናት አሉ)
.
.
ከመንግሥት ጋር በተፈጠረው ያለመግባባት ዳግም በውጊያና የተለያዩ ግጭቶች ላይ የቆየው የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት የከበረውን የገዳ ሥርዓት መርሖዎችና ሕጎች መሰረት አድርጎ ለቀረበው ጥሪና የሰላም አዋጅ ላለፉት ሶስት ቀናት ሲደረግለት የቆየው አቀባበል ትላንት ምሽት 12:00 ላይ መጠናቀቁን የእርቀ ሰላሙ የቴክኒክ ኮሚቴ ይፋ አድርጓል።

በመንግሥት እና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት መካከል እርቀ ሰላም ለማውረድ፤ በኦሮሚያ አባገዳዎች፣ በሀደ ሲንቄዎች(Haadha Siinqee)፣ በአገር ሽማግሌዎች፣ በምሁራንና ለሰላም መስፈን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሲያደርጉ በቆዩ በርካታ ዜጎች እንቅስቃሴ ጥረቱ መልካም ፍሬ አፍርቶ #በጫካ የነበረው ሠራዊት ላላፉት ሦስት ቀናት በኦሮሚያ 12 ዞኖችና 22 ወረዳዎች አቀባበል ሲደረግለት ቆይቷል።

ጥር 14 ቀን 2011 ዓ.ም በአምቦ ዩኒቨርሲቲ በአባገዳዎች #የሰላም_አዋጅ ታውጆ የእርቀ ሰላም ኮሚቴ የተቋቋመ ሲሆን ጥሪው በጎ ምላሽ አግኝቶ ሠራዊቱ መሳርያውን ለአባገዳዎችና ለቴክኒክ ኮሚቴው በማስረከብ ባሕላዊ አቀባበል፣ ባርኮት(Muuda) እና ፍቅራዊ ክብካቤ እየተደረገለት ቆይቷል።

ከነገ ጀምሮም በተዘጋጀለት ካምፕ በመግባት በሰላም ተጠሪዎች፣ በሕግ ባለሙያዎች እና በሌሎች ምሁራን የተለያዩ ስልጠናዎች መውሰድ ይጀምራል። ከሁለት ወር በማይበልጠው በዚህ ቆይታ የሠራዊቱ አባላት እንደየፍላጎታቸው እና ችሎታቸው ስልጠና ወስደው በመስካቸው የሚመደቡ ሲሆን በቆይታቸውም በአባገዳዎች፣ በቴክኒክ ኮሚቴው አባላትና በሰላም ተጠሪዎች አያያዛቸው የሚጎበኝ ይሆናል።

እስካሁን በነበረው ሂደትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የቴክኒክ ኮሚቴው የፊታችን እሁድ ተገናኝቶ አጠቃላይ ምክክርና ግምገማ የሚያደርግ ሲሆን ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

በተያያዘ ዜና -- በ'ልዩ ሁነት' በቀነ ገደቡ መግባት ላልቻሉ የሠራዊቱ አባላት ተጨማሪ #አምስት ቀን የተሰጠ ሲሆን በእነዚህ ጊዜያት በየወረዳው የሰላም ክፍሎች በመገኘት #መሳርያቸውን ማስረከብና ወደካምፕ ገብተው ለቀጣይ ሰላማዊ ሕይወታቸው ጠቃሚ የሆኑትን #ስልጠናዎች መውሰድ እንደሚችሉ ተገልጿል።

Via Gulale Post
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ባህር ዳር-የሰላም ዋጋ ስንት ነው?🔝

በዛሬው ዕለት #በባህርዳር ከተማ "የሰላም ዋጋ ስንት ነው?" በሚል የጎዳና ላይ #የሰላም_ጉባኤ ተካሂዷል።

Via NAH(TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የTIKVAH ETHIOPIA #የሰላም እና #የፍቅር አምባሳደሮች በነገው ዕለት #አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ፦

(StopHateSpeech)

1. አቅለሲያ ሲሳይ
2. የምስራች ጋሻው
3. በረከት ጉዲሳ
4. ቢንያም ይርጋ
5. ዱሬሳ በዳሶ
6. እዩኤል በቀለ
7. እዮብ ተስፋዬ
8. ቤቴል አባይነህ
9. ፍላጎት ጥላሁን
10. ሀያት እንድሪስ
11. አዚዛ እንድሪስ
12. ቤተልሄም ሴታ
13. አዲስወርቅ ተክሊ
14. ጉተማ ብርሃኑ
15. ፉአድ ኑሪ
16. አበበ ከበደ
17. ሲሳይ ታደሰ
18. ይድነቃቸው አዳነ
19. ዳንኤል ጥበቡ
20. ንብረት አበበ
21. ዮርዳኖስ ግርማ
22. ቤተልሄም እንዳልክ
23. ፍሬህይወት ማቴዎስ
24. ቃልኪዳን አክሊሉ
25. ሳሮን ገ/መድን
26. ገመቺስ ፍቃዱ
27. ሙልጌታ አደሩ
28. ምሩፅ ደማሶ
29. ቤተልሄም ቱሉ

ትሩ ላይፍ የኪነጥበብ ክበብ፦

•4 የውዝዋዜ አቅራቢዎች
•2 ገጣሚያን

ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ፦

•የተማሪዎች ህብረት ፕሬዘዳት(ወጣት ዘገየ)

#አርባምንጭ ተዘጋጁ...

እኛ ኢትዮጵያ ልጆች ነን!
እኛ የአንድነት ልጆች ነን!
ከጥላቻ ንግግሮች እንቆጠብ!

#StopHateSpeech

በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች እንመጣለን!
#TIKVAH_ETHIOPIA - እኛ ከጥላቻ የነፃን፤ ሰውነትን ያስቀደምን #የፍቅር እና #የሰላም አምባሳደሮች ነን!!

አርባምንጭ...🔄
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወደሰላም አምባሳደር ተቋም #ሀዋሳ_ዩኒቨርሲቲ የሚጓዙ የTIKVAH-ETH #የሰላም እና #የፍቅር አምባሳደሮች #ምድብ_1

•ጊዜው ጌትነት
•ወንድማገኝ ብርሃኔ
•ቤተልሄም አዱኛ
•ዱሬሳ በዳሶ
•ትግዕሥት ተስፋዬ
•ዮርዳኖስ ግርማ
•ፍሬህይወት ማትያስ
•ቤተልሄም ገ\መድን
•ቤተልሄም ሴታ
•አበባ በቃና
•ራህመት አብዱልቃድር
•ቤተልሄም ቱሉ
•ሀያት እንድርያስ
•ቤተል አባይነህ
•እዮብ ተስፋዬ
•ነብያት ዘውዱ
•እዩኤል በቀለ
•ፍቅርተ ዋለልኝ
•ቢንያም ይርጋ
•ፍላጎት ጥላሁን
•ናርዶስ ዮሃንስ
•ቃልኪዳን አክሊሉ
•ቤተልሄም እንዳልክ
•ገመቺስ ፍቃዱ
•ምሩፅ ደምሴ
•ሙልጌታ አደሩ
•ዳንኤል ተሾመ
•ፍሬዘር ገዛኸኝ
•ጉተማ ብርሃኑ
•ሲሳይ ታደሰ
•በረከት ጉዲሳ
•አቅለሲያ ሲሳይ
•የምስራች

√ 19 ሴት
√ 15 ወንድ

የተማሪዎች ህብረት ተወካዮች
የሰላም ፎረም ተወካዮች

#WSU #StopHateSpeech

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምድብ ሁለት!

ወደሰላም አምባሳደር ተቋም #ሀዋሳ_ዩኒቨርሲቲ የሚጓዙ የTIKVAH-ETH #የሰላም እና #የፍቅር አምባሳደሮች #ምድብ_2

(AMU)

•አስቻለው ደቻሳ
•ተመስገን አየለ
•መሰረት መኮንን
•ደብረወርቅ ተስፋዬ
•ቤተልሄም ዘመኑ
•ኤልያስ ምስጋና
•ማሃሪ ዳርሰማ
•ሳምራዊት ሀጎስ
•እሌኒ ነጋልኝ
•ታሪኩ ተሾመ
•የምስራች ይቆየኝ
•ጣነሮ ሁሴን
•ሀብታሙ አማረ
•ልኡል ሽመልስ
•ሀብታሙ ይልማ
•ሀብታሙ አጌና
•ቢቂላ መኮንን
•አቤል ተስፋሁን
•አዲሱ ፍስሃ
•ብሩክ አበራ
•ልኡል ዩሴፍ
•ሰለሞን አማረ
•ምስራቅ በዛብህ
•መልካሙ ማትዮስ
•ጌትነት ላይኔ
•ሙላለም እንዳሻው
•ሲሳይ አድኖ
•ዮናታን አልዮ
•አማረ ባሻ
•ተመስገን ኢሳያስ
•ኢማን መሃመድ
•ታምራት ፈረደ
•አዲሱ
•አሜን ላየ
•አዳነ ጌቱ

√ 8 ሴት
√ 29 ወንድ

የተማሪዎች ህብረት ተወካዮች
የሰላም ፎረም ተወካዮች

#AMU #StopHateSpeech

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምድብ ሶስት!

ወደሰላም አምባሳደር ተቋም #ሀዋሳ_ዩኒቨርሲቲ የሚጓዙ የTIKVAH-ETH #የሰላም እና #የፍቅር አምባሳደሮች #ምድብ_3

•አሸናፊ በቀለ
•መዝገቡ ተስፋዬ
•መሀመድ ሚፍታ
•አበበ በላቸው
•አብዱረዛቅ ኑርሰፋ
•አቤል እርቅ ይሁን
•አዳነ ለገሰ
•ናትናኤል ሰለሞን
•ዳዊት ፍቅሩ
•ፍሬው ጌታቸው
•ተምኪን ኑረዲን
•እሱባለው መረጃ
•ቃለአብ ዘበነ
•ደሳለኝ ንዳ
•እስከዳር ታደሰ
•ዮሴፍ ኃይሉ
•አስቻለው ጌቱ
•ይትባረክ አለባቸው
•ዮሃንስ አበራ
•ታዲዮስ ደጉ
•ብርሀኑ አወቀ
•ናትናኤል መርከቡ
•በእምት ሰሎሞን
•ታምራት በሻዳ
•ኑርሁሴን ከማል
•አላዛር ሲሳይ
•ሀናን በድሩ
•ማህሌት ተፈራ
•መቅደስ መሰለ
•ፌቨን ሻውል
•ሜሮን ረዳይ
•ምኞት ወርቁ
•ሰሚራ ሸረፍ
•ሀያት ሳቢር
•ፎዚያ መካ
•ፊሩዛ ሙሀበድ
•ራሄል በላቸው
•ራሄል ሰው መሆን
•ሲትሬላ ሙሀመድ
•ሰሚራ ሸረፋ
•ፈቲያ አሚን
•ሰሚራ ተሸመ
•ሰሚራ ከድር
•ሰዓዳ ሙሳ
•ግዛት ማሞ

√26 ወንድ
√19 ሴት

#WKU #StopHateSpeech
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#TIKVAH_ETH 🇪🇹 #StopHateSpeech

•ሚያዚያ 23
•ሚያዚያ 25 እና 26

√ረቡዕ - ወሎ ዩኒቨርሲቲ
√አርብ እና ቅዳሜ - መቀለ ዩኒቨርሲቲ

ወደ #ወሎ_ዩኒቨርሲቲ እና #መቀለ_ዩኒቨርሲቲ የሚጓዙት፦

√የአርባምንጭ ዩንቨርስቲ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት

√የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት

√የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት

√የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት

ከ100 የሚበልጡ #የሰላም እና #የፍቅር አምባሳደሮች በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ይሰባሰባሉ!!

ኑ ኢትዮጵያን #በፍቅር እንገንባ!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የዋጋ ጭማሪ...

በአዲስ አበባ ከተማ በመሰረታዊ የምግብ ሸቀጦች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ መታየቱን ተከትሎ የከተማው አስተዳደር ጥናት በማድረግ እርምጃ ሊወስድ መዘጋጀቱን ገለፀ። በተለይም በአትክልት ምርቶች ላይ የታየው ጭማሪ አሳሳቢ እንደሆነ በአዲስ አበባ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ የንግድ ቁጥጥርና ክትትል የሥራ ሒደት መሪ ካሳሁን በየነ ገልጸዋል። በአገሪቱ በነበረው #የሰላም_መደፍረስ ምክንያት የአትክልት አቅራቢዎች በበልግ ወቅት በሙሉ አቅማቸው ያለማምረታቸው በክረምት ወቅት የሚያጋጥመውን የምርት እጥረት አባብሶታል ብለዋል። በተለይም መቂ ከተማን ጨምሮ በመስኖ ምርት የከተማዋን የአትክልት አቅርቦት በሚሸፍኑ አካባቢዎች ላይ የተፈጠረው ጫና የተወሰነ የምርት እጥረት አምጥቷል ቢባልም ላለፉት ኹለት ሳምንታት የታየው ጭማሪ ግን ሰው ሰራሽ ሊሆን እንደሚችል ካሳሁን ሥጋታቸውን ገልጸዋል።
.
.
“መንግሥት የገበያ ዋጋን ለማውጣት እና ለማስገደድ ሕጉ አይፈቅድለትም፣ ነገር ግን የሕዝብ ኑሮ ላይ ጫና ለመፍጠር እና ያለአግባብ ለመበልፀግ የሚደረግ አሻጥር ላይ ግን ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ጥናታችን አጠናቀናል” አቶ ካሳሁን

Via አዲስ ማለዳ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአሶሳ የሰላም አየር እየነፈሰ ነው!

አሁን በስራ ምክንያት ያለሁት በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ዋና ከተማ #አሶሳ ነው። ሞቃት የአየር ንብረት የሚስተዋልባት፣ አረንጓዴ፣ እና ቀይ ለም አፈር ያለው መሬት ያላት። አሶሳ ከመጣሁ እነሆ ሶስተኛ ቀኔ አለፈ።

አንዳንድ ጓደኞቼ እንዲሁም ቤተሰቦቼ ጋር ተደዋውዬ በስልክ ሳወራ ከኔ ሁኔታ ይልቅ ስላለሁበት ቦታ #አሶሳ አብዝተው ይጠይቃሉ። ገና ለመምጣት በነበርኩበት ግዜ እራሱ ምነው ወደዛ መሄድህ... ? በሰላም ነው? እያሉ በጥያቄ ያጨናነቁኝ ቁጥራቸው ብዙ ነው። መጠየቃቸውን እንደ መጥፎ ነገር ባልቆጥረውም አንድ ነገር ግን በአእምሮዬ ብቅ እንዲል ሆኗል። እኔ ባለሁበት ሰዐት አሶሳ እጅግ #የተረጋጋች፣ ሰላማዊ እና የዕለተ ቀን እንቅስቃሴዋን የምትከውን ከተማ ነች።

ምናልባት የሰዎች ጥያቄ የመጣው ከጊዜያት በፊት በክልሉ በመተከል፣ ካማሺ እና ሌሎች ቦታዎች ላይ በነበረው አለመረጋጋት እና ግጭት ይመስለኛል። እስካሁን ድረስ ግን ብዙ ሰዎች በክልሉ እንዲሁም በሌሎች ክልሎች ሰላማዊ ሁኔታ ያለ #አይመስላቸውም

ሰላም እና መረጋጋትም የማይመቻቸው እና እንቅልፍ የሚነሳቸው አካላት በየማህበራዊ ሚዲያው በሚፈጥሩት ዉዥንብር ምክንያት እና በማይረቡ ተናፋሽ ወሬዎች ማለቴ ነው እና አሁን በአሶሳ ፍፁም #የሰላም አየር ነው እየነፈሰ ያለው ያለው። እንዲሁ በሌሎች ክልሎችም እንዳጣራሁት ከሆነ በብዛት የተረጋጋ ሁኔታ ነው ያለው። የኢትዮጵያ ሰላም እየተመለሰ ነው። ይመለሳልም። ኢትዮጵያ በሰላም፣ እስከዘላለም ትኑር።

Y ነኝ ቤተሰባችሁ ከአሶሳ!

ፎቶ: ፋይል
@tsegabwolde @tikvahethiopia