TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Update የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን⬇️

በቡራዩና በመዲናዋ ዙሪያ ባሉ አካባቢዎች የተከሰቱ #ግጭቶች ላይ የደረሱ ሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን የሚያጣራ ቡድን #ከዛሬ ጀምሮ መሰማራቱን የኢትዮጰያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን አስታወቀ።

ኮሚሽኑ ይህንን ያለው በዛሬው ዕለት ግጭቱን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኀን በሰጠው መግለጫ ላይ ነው።

በመግለጫው ኮሚሽነር ዶክተር አዲሱ ገ/እግዚአብሄር እንደተናገሩት በደረሰው ግጭት በሰው ህይወትና አካል እንዲሁም በንብረት ላይ ውድመት መድረሱን አንስተዋል።

ግጭቱ በዚሁ ከቀጠለ #ለከፋ ጉዳት ያደርሳል ያሉት ኮሚሽነሩ መንግስት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለማስቆም እና ተዘዋውሮ የመስራት እንዲሁም በሰላም የመኖር መብቶችን ለማስከበር ጠንከር ብሎ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።

ኮሚሽኑ እስከ አሁን የደረሰውን ጉዳት መንስዔ፣ ጉዳት እና ስፋት አጣርቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሪፖርት በማድረግ ያጠፉ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ ይደረጋልም ተብሏል።

በተለያዩ ቦታዎችም የተከሰተውን ግጭት እንዲረጋጋ ከመንግስት ጋር እየሰራ መሆኑንም ኮሚሽኑ አስታውቋል።

ኮሚሽኑ በመግለጫው የፌደራል እና የክልል #ጸጥታ አካላትም ሚናቸውን #በአግባቡ እንዲወጡ አሳስቧል።

©Fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia