TIKVAH-ETHIOPIA
#እንድታውቁት🚨 የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን " አርቲሜተር " የተባለውን በመርፌ የሚሰጥ የወባ መድኃኒት ጥቅም ላይ እንዳይውል አግዷል፡፡ መ/ቤቱ ተደርጓል ባለው የገበያ ቅኝት መድኃኒቱ መገኘቱን ፣ በባለስልጣኑ ያልተመዘገበ እንዲሁም ናሙናው ተወስዶ በላብራቶሪ ሲፈተሽ አርቲሜተር (Artemether) የተባለው ንጥረ ነገር በውስጡ አለመገኘቱ መረጋገጡን ገልጿል፡፡ በዚህም ይህን መድኃኒት…
#እንድታውቁት🚨

የትኛው የወባ መድኃኒት ነው አትጠቀሙት የተባለው ?

አርቲሜተር የተባለ በመርፌ የሚሰጥ የወባ መድኃኒት /Arthemeter 80 mg/ml injection, Batch No. 231104SPF, manufacture Date; 11/2023 supplied by Shinepharm, China በተደረገ የገበያ ላይ ቅኝት የተገኘ እና በባለስልጣኑ ያልተመዘገበ እንዲሁም ከገበያም ናሙና ተወስዶ በላብራቶሪ ሲፈተሸ Arthemeter የተባለው ንጥረ ነገር በውስጡ አለመገኘቱ መረጋገጡን የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አሳውቋል።

ይህን መድኃኒት ነው የጤና ባለሙያዎች እንዳይጠቀሙት በተጨማሪም በየደረጃው ያሉ የክልል ተቆጣጣሪዎች በየአካባቢያቸው ጥብቅ ክትትል በማድረግ እርምጃዎች እንዲወስዱ ማሳሰቢያ የተላለፈው።

@tikvahethiopia