TIKVAH-ETHIOPIA
የፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የቀብር ስነ ስርዓት ነገ መስከረም 9 ይፈፀማል። ነገ ከጠዋቱ 3 ሰዓት  ሳሪስ አደይ አበባ ከሚገኘው የመኖሪያ ቤታቸው ወደ ሚሊኒየም አዳራሽ አሸኛኘት ይደረጋል። ከአራት ሰዓት ጀምሮ በሚሊኒየም አዳራሽ የተለያዩ ስነስርዓቶች ይካሄዳሉ። የቀብር ስርዓታቸው ከቀኑ 8 ሰዓት በአዲስ አበባ ብርሐናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ይፈጸማል። መረጃው የሀድያ ቴሌቪዥን ነው።…
የፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ።

የጉምቱው ፖለቲከኛ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ስርዓተ ቀብር በጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ተፈፅሟል፡፡

ከስርዓተ ቀብራቸው ቀደም ብሎ የአስክሬን ሽኝት በሚሊኒየም አዳራሽ ተካሂዷል።

በሽኝት ስነ-ሥርዓቱ ላይ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ተገኝተው ነበር።

በተጨማሪ በሆሣዕና የሀዲያ ዞንና የአከባቢው ህዝብ በፕሮፈሰር በየነ ጴጥሮስ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ሀዘን በኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ አደባባይ በመገኘት ሲገልጽ ውሏል።

@tikvahethiopia