TIKVAH-ETHIOPIA
🔈#የነዋሪዎችድምጽ • “ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የሚተገበረው ግን መቼ ነው ? ” - የቡለን ወረዳ ነዋሪዎች • “ ‘ለምን አልመርጣችሁኝም ’ በማለት በበቀል ህዝብን መጉዳት ተገቢ አይደለም ” - ዶ/ር መብራቱ አለሙ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ቡለን ወረዳ ‘ ለምን ፓርቲውን መረጣችሁ ’ በሚል ሰበብ በደል እየደረሰባቸው መሆኑን የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አባላት እና ፓርቲው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ…
" ከምርጫ ወዲህ ከፍተኛ ጫና እየደረሰብን ነው " - ቦሮ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚንቀሳቀሰው የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የፖለቲካ ድርጅት ሰኔ 16 ቀን፣ 2016 ዓ.ም በክልል ምርጫ ከተካሄደ ወዲህ በፓርቲው ላይ ከፍተኛ ጫና እንደደሰበት እንደሚገኝ አሳውቋል።

ፓርቲው ምን አለ ?

- መተከል ዞን 3 ለክልል ምክርቤት እና አንድ የህዝብ ተወካዩች ምክርት ቤት ወንበር ማግኘት ችለናል።

- በቡሌን ወረዳ " ተቃዋሚ ፓርቲ መርጣቹሀል " ተብሎ የፓርቲው ደጋፊዎች ፣ነጋዴዎችና አርሶ አደሮች ላይ ዛቻ እና ማስራርያ እየደረሰ ይገኛል። የፓርቲ አባላትም ለእስር እየተዳረጉ ይገኛሉ።

- የተቀናጀ ወከባና ዛቻ ነው የሚደርሰው። በተለይ ከምርጫው ውጤት በኃላ።

- ቡሌን ወረዳ ላይ አባላት በተለያዩ ወቅቶች ይታሰራሉ። ከልዩ ልዩ የፖለቲካ እና ማህበራዊ ተሳትፎ ተከልክለዋል። በንግድ፣በግብርና እንዲሁም በመንግስት ስራ ላይ የተሰማሩ የፓርቲው ደጋፊዎች ላይ " ተፎካካሪ ፓርቲ ደግፋቹሀል፣ መርጣቹሀል " በሚል ማስፈራሪያና ዛቻ ይደርሳል።

- የፓርቲውን አባላት መብት በመንፈግ የፖለቲካ አመለካትን መሰረት ያደረገ ጫናዎች እየደረሱ ነው።

- በፓርቲው ላይ የደረሱ የመብት ጥሰቶችን የሰብአዊ መብት ተቋማት ሊከታተሉት ይገባል።

የቡሌን ወረዳ ፖሊስ ለቀረበው ክስ ምን ምላሽ ሰጠ ?

የፖሊስ ፅ/ቤት አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ብርሀኑ ኤጄታ ፦

" በወረዳው በፖለቲካ አመለካከቱ የታሰረ ሆነ በደል የደረሰበት ግሰለብም ሆነ ቡድን የለም።

በአካባቢው የፖለቲካ ድርጅቶች ሰላማዊ በሆነ መንገድ በምርጫ ተሳትፈዋል።

ፓርቲው ያቀረበው ቅሬታ ተቀባይነት የሌለው ክስ ነው። " #ዶቼቨለ

@tikvahethiopia