#ጥቆማ #ጥንቃቄ 🚨

ይህ የተንጋደደና ለመውደቅ ጫፍ የደረሰ የመንገድ መብራት ምሰሶ ወድቆ በአስፓልቱ ላይ በሚተላለፍ ተሽከርካሪ እና በሰው ላይ ጉዳት ከማድረሱ በፊት መፍትሄ ይፈለግለት።

ይነሳ አልያም በአግባቡ ይጠገን።

ቦታው አዲስ አበባ ፣ ከአትላስ ወደ ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን መሄጃ የትራፊክ መብራቱ ጋር ነው።

እንዲሁ ሊወድቅ እንዳለና እንደተንጋደደ በርካታ ቀናት የተቆጠሩ ሲሆን የሚያነሳው እና የሚያስተካክለው አልመጣም።

ከከባዱ የክረምት ወቅት ጋር ተያይዞ ወድቆ ጉዳት ሳይደርስ በፊት አስቸኳይ መፍትሄ ይሰጠው።

👉 ለአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ
👉 ትራፊክ ማኔጅመንት

#TikvahEthiopiaAddisAbaba

@tikvahethiopia