የNGAT ፈተና መቼ ይሰጣል ?

ትምህርት ሚኒስቴር ፥ የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ተጨማሪ የምዝገባ ጊዜ እና የፈተና ቀንን አሳውቋል።

በ2017 የትምህርት ዘመን የድህረምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ያላቸው እና በተለያዩ ምክንያቶች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ ያመለጣቸው አመልካቾች እስከ ነሐሴ 26/2016 ዓ.ም ድረሰ በ https://ngat.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ ይችላሉ ብሏል።

ለፈተናው የተመዘገቡ በየተመደቡበት የፈተና ማዕከላት እና የመፈተኛ ፕሮግራም መሰረት ከነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ፈተናው እንደሚሰጣቸው ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

ተፈታኞች በፈተና ወቅት የተሰጣቸውን User Name and Password፣ እና ማንነታቸውን የሚገልጽ መታዋቂያ ይዘው መቅረብ እንዳለባቸው ማሳሰቢያ ተላልፏል።

#MoE

@tikvahethiopia