TIKVAH-ETHIOPIA
 #TPLF : የህወሓት የፅህፈት ቤት ሃላፊና የጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/ብሔር  የህወሓት ማእከላዊ  የቁጥጥር ኮሚሽን አባላት በጉባኤ እንዲሳተፉ በፃፉት ደብዳቤ " 14ኛው የህወሓት ጉባኤ ነሃሴ 7/2016 ዓ.ም ከጥዋቱ 3:00  ጀምሮ በመቐለ የሰማእታት ሓወልት አዳራሽ ይካሄዳል " ይላል። ይሁን እንጂ የደርጅቱ ማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን ከ2 ሳምንት በፊት ከሚካሄደው ጉባኤ ራሱ…
#TPLF

ሰባት የመቐለ ከተማና ሁለት የትግራይ ማእከላዊ ዞን ከፍተኛ ካድሬዎች " ጠባብ ቡድን " ሲሉ በጠሩ አካል ተጠርቷል ባሉት የህወሓት ጉባኤ እንደማይሳተፉ አስታወቁ።

አመራሮቹ ፤ " ባሁኑ ወቅት የሚካሄደው ጉባኤ ከጥቅሙ ጉዳቱ ስለሚያመዝን ላለመሳተፍ ወስነናል " ብለዋል።

በጉባኤው እንዳማይሳተፉ በደብዳቤ ያስታወቁ የህወሓት ከፍተኛ ካድሬዎች ፦

1. ነጋሽ ኣርኣያ - የመቐለ ጀተማ የህወሓት ፅህፈት ቤት ሃላፊ 
2. ሓለፎም ገ/ህይወት  - የሓድነት ክፍለ ከተማ ዋና አስተዳዳሪ (መቐለ)
3. ኤልያስ ኪሮስ  -  የዓዲ ሓቂ ክፍለ ከተማ ዋና አስተዳዳሪ (መቐለ)
4. እያሱ ተካ  -  የዓይደር ከፍለ ከተማ ዋና አስተዳዳሪ (መቐለ)
5. ኣስመላሽ ብርሃኑ  - የዓዲ ክፍለ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ (መቐለ)
6. ፍጹም ለገሰን - በትግራይ ማእከላዊ ዞን የዓዴት ወረዳ አስተዳዳሪ 
7. ሓጎስ ንጉስ - የዓዴት ወረዳ የአደረጃጀት ሃላፊ ናቸው።

@tikvahethiopia