#TPLF
ሰባት የመቐለ ከተማና ሁለት የትግራይ ማእከላዊ ዞን ከፍተኛ ካድሬዎች " ጠባብ ቡድን " ሲሉ በጠሩ አካል ተጠርቷል ባሉት የህወሓት ጉባኤ እንደማይሳተፉ አስታወቁ።
አመራሮቹ ፤ " ባሁኑ ወቅት የሚካሄደው ጉባኤ ከጥቅሙ ጉዳቱ ስለሚያመዝን ላለመሳተፍ ወስነናል " ብለዋል።
በጉባኤው እንዳማይሳተፉ በደብዳቤ ያስታወቁ የህወሓት ከፍተኛ ካድሬዎች ፦
1. ነጋሽ ኣርኣያ - የመቐለ ጀተማ የህወሓት ፅህፈት ቤት ሃላፊ
2. ሓለፎም ገ/ህይወት - የሓድነት ክፍለ ከተማ ዋና አስተዳዳሪ (መቐለ)
3. ኤልያስ ኪሮስ - የዓዲ ሓቂ ክፍለ ከተማ ዋና አስተዳዳሪ (መቐለ)
4. እያሱ ተካ - የዓይደር ከፍለ ከተማ ዋና አስተዳዳሪ (መቐለ)
5. ኣስመላሽ ብርሃኑ - የዓዲ ክፍለ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ (መቐለ)
6. ፍጹም ለገሰን - በትግራይ ማእከላዊ ዞን የዓዴት ወረዳ አስተዳዳሪ
7. ሓጎስ ንጉስ - የዓዴት ወረዳ የአደረጃጀት ሃላፊ ናቸው።
@tikvahethiopia