TIKVAH-ETHIOPIA
#ዕለታዊ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዛሬው የምንዛሬ ዋጋ ስንት ነው ? 💵 US Dollar #CASH Buying ➡️ 74.7364 Selling ➡️ 76.2311 #TRANSACTION Buying ➡️ 74.7364 Selling ➡️ 76.2311 💷 Pound Sterling #CASH Buying ➡️ 91.5537 Selling ➡️ 93.3848 #TRANSACTION Buying ➡️ 96.0811 Selling…
#ዕለታዊ : የዶላር ዋጋ ጨምሯል።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንዱ የአሜሪካ ዶላር በ77 ብር ከ1280 ሳንቲም እየተገዛ በ78 ብር ከ6706 ሳንቲም እየተሸጠ ይገኛል።

ፓውንድ ስተርሊንግ በተመሳሳይ ጨምሯል።

አንዱ በፓውንድ በ94 ብር ከ3071 ሳንቲም እየተገዛ በ96 ብር ከ1932 ሳንቲም እየተሸጠ ነው።

ትላንት መጠነኛ መውረድ አሳይቶ የነበረው ዩሮ ዛሬ ጨምሮ አድሯል። አንዱ ዩሮ በ83 ብር ከ3754 ሳንቲም እየተገዛ በ85 ብር ከ0429 ሳንቲም እየተሸጠ ነው።

ከመንግስታዊ ባንክ ውጭ በግል ባንኮችም የዶላር ዋጋ ጨምሯል።

ለአብነት ወጋገን ባንክ አንዱን የአሜሪካ ዶላር በ77 ብር ከ7401 ሳንቲም እየገዛ በ79 ብር ከ2949 ሳንቲም እየሸጠ ነው።

ዩሮ 82 ብር ከ6591 ሳንቲም እየገዛ በ84 ብር ከ3123 ሳንቲም እየሸጠ ሲሆን ፓውንድ ስተርሊንግ በ93 ብር ከ6991 ሳንቲም እየገዛ በ95 ብር ከ5731 ሳንቲም እየሸጠ ነው።

በአንጻሩ ኦሮሚያ ባንክ ዶላርን ጨምሮ ዩሮ እና ፓውንድ ስተርሊንግ ትላንት ሲጠቀምበት በነበረው ተመን ነው ዛሬም የቀጠለው።

በዚህም አንዱ ዶላር በባንኩ በ74 ብር ከ7382 ሳንቲም እየተገዛ በ76 ብር ከ2329 ሳንቲም እየተሸጠ ነው።

ዩሮ በ81 ብር ከ0386 እየተገዛ በ82 ብር ከ6593 ሳንቲም እየተሸጠ ይገኛል።

ፓውንድ ስተርሊንግ በ92 ብር ከ6021 ሳንቲም እየተገዛ በ94 ብር ከ4542 ሳንቲም እየተሸጠ ነው።

በገበያ ላይ የተመሰረተ የውጭ ምንዛሬ ተመን / Floating exchange rate ወይም ባንኮች ከደንበኞቻቸው ጋር በሚያደርጉ ነጻ ድርድር የውጭ ምንዛሬ መግዛት እና መሸጥ እንዲችሉ የሚፈቅደው አሰራር ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ባንኮች የየራሳቸውን ዕለታዊ ምንዛሬ አውጥተው እየተጠቀሙ ናቸው።

ዝርዝር ዕለታዊ ምንዛሬ ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia