🔈#የእገዛጥሪ

" ወንድማችንን ታደጉልን ! " - ጓደኞቹ

አቤል ተሾመ (ናቲ ) ከ1 አመት በፊት ( 2015 ሀምሌ ) በClinical Pharmacy ከሐረር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በከፍተኛ መዓረግ መመረቁን ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ ይናገራሉ።

ከዛሬ 7 ወር በፊት በድንገኛ  አጣዳፊ የኩላሊት ጉዳት (Acute kidney injury) እና የደም ግፊት ፣ ገለምሶ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ወዲያው ወደ ጥቁር አንበሳ ሪፈር ይባላል።

በጥቁር አንበሳ የውስጥ ደዌ ፣ የኩላሊት ስፔሻሊቲ ንዑስ ክፍል (Nephrology Department ) ላለፉት 7 ወራት የህክምና ክትትል ሲያረግ ጎን ለጎንም ላለፉት 3 ወራት በመቻራ ( ዳሮ ለቡ ) ሆስፒታል በተመረቀበት ሞያ ህዝቡን እያገለገለ ነበር።

ከወር በፊት ግን ህመሙ ከቁጥጥር ውጭ ሆኖ ክትትል በሚያረግበት ክፍል፣ የኩላሊቶቹ ጉዳት የመጨረሻ ደረጃ End stage renal disease እንደደረሰ እናም የኩላሊት እጥበትና ንቅለ-ተከላ እንደሚያስፈልገው እንደተረገረው አስረድተዋል።

ለዚህም ህክምና ቢያንስ እስከ 2 ሚሊየን እና ከዚያም በላይ እንደሚያስፈልገው ተገልጾለታል።

" አሁን ላይ ወደ ቅዱስ ጷውሎስ ተዘዋውሮ የቅድመ ንቅለ ተከላ ሂደት ጀምሯል " ያሉት ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ " ሆኖም የዚህ ህክምና ወጪ ከአንድ ፋርማሲስት ( Pharmacist ) እና መንግስት ሰራተኛ ቤተሰቡ አቅም በላይ ስለሆነ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በቻለው አቅም እንዲደግፈው " ሲል ተማጽነዋል።

የሒሳብ ቁጥር የአባቱ 1000055784772 Teshome Nigusse (CBE)  እንዲሁም የራሱ 1000055874895 Abel Teshome (CBE) እንደሆነ ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM