TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በሲዳማ ክልል በወንሾ ወረዳ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ የሞቱ ወገኖቻችን ቁጥር 9 ደርሷል። 6 ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በይርጋለም ሆስፒታል ይገኛሉ። በሌላ በኩል ፤ በዛው ሲዳማ ክልል በቡራ ወረዳ በድንገተኛ ውኃ ሙላት የሁለት ሕጻናት ሕይወት አልፏል። #ኤፍቢሲ @tikvahethiopia
#Sidama

በሲዳማ ክልል፣ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት እና የውሀ ሙላት አደጋ የሞቱ ዜጎች 11 መሆኑን የሲዳማ ክልል አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አበራ ዊላ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ከዚህ ውስጥ ዘጠኙ የሁለት አባወራ ቤተሰቦች ሲሆኑ አንዱ 5 አንዱ ደግሞ 3 ቤተሰቦቻቸዉን ማጣታቸውን ገልጸዋል።

አንድ ግለሰብ ከገበያ ሲመለስ ከተራራ የወረደ ናዳ ላዩ ላይ በማረፉ ለህልፈት እንደዳረገው ገልጸዋል።

ከዚህም በተጨማሪ ደግሞ በቡራ ወረዳ ወንዝ ሞልቶ ከአቅጣጫው ውጭ በመፍሰስ በአካባቢዉ ያለ ቤት ውስጥ በመግባት 2 ልጆችን ህይወት መቅጠፉን ተናግረዋል።


ከአካባቢው ተራራማነትና ያለማቋረጥ ከዘነበው ዝናብ ጋር ተያይዞ አሁን ላይ ተጨማሪ አደጋዎች ይከሰታሉ ተብሎ ስጋት አለ።

ይህንንም ተከትሎ ከክልሉ የጸጥታ ቢሮ ፣ የጤና ቢሮና ሌሎች ተቋማት የተወጣጣ ግብረሀይል ተቋቁሞ ወደስራ ተገብቷል ብለዋል።

" ስጋት ያለባቸው አካባቢዎች ናቸው " ተብለው ከተለዩ ስድስት ወረዳዎች የሚኖሩ ዜጎችን የማውጣት ስራ መጀመሩን ጠቁመዋል።

ከቀያቸዉ ከተነሱትን ራቅ ያለ ቦታ ዘመድ ያለው ወደዛ ሲሄድ ሌሎች በት/ቤቶች ፣ በቤተእምነቶችና መሰል ቦታዎች እየተጠለሉ መሆኑን ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaHW

@tikvahethiopia