TIKVAH-ETHIOPIA
#EthiopianAirlines🇪🇹 " የኤርትራ ሲቪል አቬሽን ውሳኔውን መልሶ እንዲያጤነው እንጠይቃለን ፤ ይህ የማይሆን ከሆነ የሚጎዱት ወደ ኤርትራ የሚጓዙ ተጓዦች ናቸው " - " አቶ መስፍን ጣሰው የኤርትራ ሲቪል አቬሽን ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ የሚያደርገው በረራ ከመስከረም 30 / 2024 ጀምሮ እንዲቆም የሚያሳውቅ ደብዳቤ መላኩን ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው…
#Ethiopia : የኢትዮጵያ አየር መንገድ በህይወት ያሉ እንሰሳትን በማጓጓዝ ላይ ስለሚቀርበው ቅሬታ ምን ምላሽ ሰጠ ?

የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ፦

" ይህ ጉዳይ ዓለም አቀፍ አሰራር ስለሆነ መስፈርቱን ጠብቀን አገልግሎቱን እንሰጣለን።

ጫጩት እናጓጉዛለን፤ በጎች የምናጓጉዝበት ጊዜ ነበረ፤ ፍየሎች እናጓጉዛለን። በአንድ ወቅት አሁን እንኳን አይደለም ላሞችና በሬዎች በህይወት እያሉ እናጓጉዝ ነበረ።  አሁን ዝንጀሮዎች አጓጓዛችሁ ነው የሚሉን።

ህጋዊ ፈቃድ የተሰጠው ከአሜሪካም ከሌላም ሀገር ህጋዊ ፈቃድ የተሰጠው ድርጅት እስከመጣ ድረስ ያንን የዓለም አቀፍ ህጉን ተከትለን እናጓጉዛለን።

ጥያቄ የእንስሳት ተቆርቋሪ ነን የሚሉ አካላት ናቸው የሚያነሱት መነሻቸው ' ዝንጀሮዎቹ  ወደ እዛ ሄደው ለላብራቶሪ አገልግሎት ነው የሚውሉት ' የሚል ነው። ይሄ ግን ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ኃላፊነት አይደለም።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የንግድ ተቋም ነው እንደ ንግድ ተቋም ነው የሚሰራው። "


#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia