#USA
" ካማላ ሃሪስ ዕጩ ሆነው እንዲቀርቡ ድጋፍ እሰጣለሁ " - ባይደን
ፕሬዜዳንት ጆ ባይደም ከአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ራሳቸውን ማግለላቸውን በይፋ አሳውቀዋል።
ባይደን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እራሳቸውን ከምርጫው እንዲያገሉ ጫና ሲደረግባቸው እንደነበእ ይታወሳል።
ዛሬ ምሽት " ለፓርቲዬ እና ለሀገሬ ጥቅም ሲባል ራሴን ከ2024 ፕሬዝዳንተዊ የምርጫ ፉክክር አውጥቻለው " ሲሉ በይፋ ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንት ባይደን፤ ምክትል ፕሬዝዳንት ካማላ ሃሪስ የዴሞክራቶች ዕጩ ሆነው በፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ እንዲቀርቡ ድጋፍ ሰጥተል።
" እኔን ተክተው ካማላ ሃሪስ ለፕሬዝዳንት እንዲወዳደሩ እፈልጋለሁ " ብለዋል።
ከቀናት በፊት የቀድሞው የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ትራምፕ የሪፐብሊካን ፓርቲ ዕጩነታቸውን በይፋ መቀበላቸው አይዘነጋም
@tikvahethiopia