TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሀገር መከላከያው ስለ ትግራይ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ የማድረግ እንቅስቃሴ ምን አለ ? የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌ/ጄነራል ብርሃኑ በቀለ ከብሄራዊ ቴሌቪዥን ጋር ቆይታ አድርገው ነበር። የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነትን መሰረት በማድረግ በጦርነቱ የተፈናቀሉ ዜጎችን የመመለስ ስራ እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል። ሀገር መከላከያው ተፈናቃዮችን የመመለስ ስራ እንዲያስተባብር አቅጣጫ…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ ፦ በጦርነት ከፀለምት እና አካባቢው ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉትን ወገኖች ወደ ቄያቸው የመመለስ ስራ እየተሰራ ይገኛል።

በርካታ የህዝብ ማመላለሻ መኪናዎች ተፈናቃዮችን እያደረሱ ነው።

የሀገር መከላከያ ሰራዊት ተፈናቃዮችን ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ የማስተባበር ኃላፊነት እየተወጣ ነው።

በፀለምት ውስጥ ካሉ 25 ቀበሌዎች በአብዛኛው ከ22ቱ ዜጎች ተፈናቅለዋል።

እነዚህን ዜጎችን ነው በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ የማድረግ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ የተገለጸው።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በቀጣይም የሌሎች አካባቢዎች ተፈናቃዮች እንደሚመለሱ አሳውቋል።

Video Credit - DW

@tikvahethiopia