TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray በትግራዩ ጦርነት ምክንያት በየቦታው የተቀበሩ እና የተጣሉ ተተኳሾች፣ ፈንጂዎች አሁንም በሰው ህይወት ላይ አደጋ ማድረሳቸው ቀጥሏል። ዛሬ ዓርብ ግንቦት 16 / 2016 በተጣለ ተተኳሽ ባል እና ሚስት ህይወታቸው አልፏል። አደጋው ያጋጠመው በትግራይ ክልል ፣ በማእከላዊ ዞን ቆላ ተምቤን ምረረ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ሲሆን በተተኳሹ ምክንያት የባል ህይወት ወድያው አልፏል። የሟች ሚስት ወደ…
#Tigray🚨

በሓውዜን ወረዳ በተጣለ ተተኳሽ #የ4_ሰዎች ህይወት ጠፋ።
 
በትግራዩ ጦርነት ምክንያት በየቦታው የተቀበሩ እና የተጣሉ ተተኳሾች ፣ ፈንጂዎች አሁንም በሰው ህይወት ላይ አደጋ ማድረሳቸው ቀጥሏል።

ሰኔ 1/2016 ዓ.ም በትግራይ ክልል በምሰራቃዊ ዞን ፤ ሓውዜን ወረዳ ማይጎቦ ቀበሌ ገበሬ ማህበር በፈነዳ ተተኳሽ የ4 ወገኖች ህይወት #ተቀጥፏል።

ከአራቱ የአደጋው ሰለባዎች ሶስቱ የአንድ ቤተሰብ አባል ናቸው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሓውዜን ወረዳ ኮሙኒኬሽን ባገኘው መረጃ  ፥ ሟቾቹ ከ 9 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ገና ትንንሽ ልጆች ናቸው።

ከሰላም ስምምነቱ በኋላ የሰኔ 1/2016 ዓ/ም አደጋን ጨምሮ በትግራይ የተለያዩ ወረዳዎች በተጣሉ እና በተቀበሩ  ተተኳሾችና ፈንጂዎች ከ107 ሰዎች ላይ የሞት ፣ የአካል መጉደል አደጋ ደርሷል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia