#Ethiopia

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኢንጂነር አይሻ መሀመድ እና ዶ/ር አብርሃም በላይን የስልጣን ቦታ ቀያየሩ።

ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሹመት ሰጥተዋል።

በዚህም ፦

1. ኢንጂነር አይሻ መሀመድ የመከላከያ ሚኒስቴር ሚንስትር ፣

2. ዶ/ር አብረሃም በላይ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚንስትር ፣

3. ዶ/ር መሀመድ እንድሪስ ደግሞ በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አድርገው ሾመዋቸዋል።

ኢ/ር አይሻ መሀመድ በ2011 ዓ/ም የመጀመሪያዋ ሴት የሀገር መከላከያ ሚኒስትር ሆነው ከተሾሙ በኃላ 6 ወር እንዳገለገሉ ከቦታው ተነስተዋል።

ዶ/ር አብርሃም በ2014 ነበር የመከላከያ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት።

ዶ/ር አብርሃም በላይ የአሁኑ ሹመት እስኪሰጥ ድረስ ሀገር መከላከያ ሚኒስቴርን በሚኒስትርነት እያገለገሉ የነበሩ ሲሆን አሁን በኢ/ር አይሻ መሀመድ ተተክተው የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ሆነዋል።

@tikvahethiopia