" በቴክኒካል ብልሽት የዲጅታል አገልግሎት ተቋርጧል " - CRRSA

የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ፤ በዋና የከተማው መረጃ ማዕከል ላይ የቴክኒካል ብልሽት እንዳጋጠመው አሳውቋል።

በዚህም ምክንያት የዲጂታል አገልግሎቱ ከትላንት ጀምሮ እንደተቋረጠ ገልጿል።

ከከተማው የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እንዲሁም ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በጋራ ጥገና በማድረግ ለመፍታት ጥረት እያደረገ እንደሆነም አስረድቶ ነዋሪዎች በትዕግስት እንዲጠባበቁ ጠይቋል።

@tikvahethiopia