#Attention

የማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖስት ፤ ከዛሬ ጀምሮ የትኛውም አይነት የትራንስፖርት አገልግሎት ከደሴ - ሸዋሮቢት_ ደ/ብረሀን እንዲሁም ከደ/ብረሀን -ሸዋሮቢት - ደሴ እንዲቆም ውሳኔ መተላለፉን አሳውቋል።

የትራንስፖርት እንቅስቃሴው እንዲቆመ የተደረገው ኮማንድ ፖስቱ " ፅንፈኛ " ባላቸው ታጣቂዎች ላይ ኦፕሬሽን በመጀመሩና ቀጠናውን ነፃ ለማድረግ እርምጃ መውሰድ በመጀመሩ እንደሆነ ተገልጿል።

በመሆኑም በቀጠናው የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲቆም የተወሰነው ሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ መሆኑን ያሳወቀው ኮማንድ ፖስቱ ውሳኔው ለጊዜው ነው ብሏል።

ህብረተሰቡ ከዛሬ ጀምሮ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ #እንዲቆም የተወሰነ መሆኑ እንዲያውቅና አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ፤ የፀጥታ ሀይሉም ውሳኔው እንዲፈፀም ክትትል እንዲያደርግ ትዕዛዝ መሰጡቱ ታውቋል።

@tikvahethiopia