ኢትዮ ቴሌኮም

የዘመናችንን መጨረሻውን የ5ኛ ትውልድ ኔትወርክ አገልግሎት በሐረር እና ሀሮማያ ከተሞች በይፋ ማስጀመራችንን ስናበስር እጅግ ደስ ይለናል!

አገልግሎቱን ከትናንት በስቲያ በድሬዳዋ ከተማ እንዲሁም ቀደም ሲል በአዲስ አበባ፣ አዳማ እና ጂግጂጋ ከተሞች ማስጀመራችን ይታወሳል።

የ5ጂ የሞባይል ኔትወርክ ወሳኝ ለሆኑ፣ በከፍተኛ ቅጽበት፣ ፍጥነትና በተመሳሳይ ወቅት (real-time) መከወን ላለባቸው ማኑፋክቸሪንግ፣ ጤና ፣ ትምህርት፣ ትራንስፖርት፣ ግብርና፣ ስማርት ሆም፣ ለብሮድካስቲንግ፣ በክላውድ ላይ ለተመሰረቱ የ5ጂ ጌሞች እንዲሁም የIOT ቴክኖሎጂዎች እውን ለማድረግ አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡

የህዝባችንን ኑሮ በእጅጉ የሚያሻሽል፣ የደንበኞችን ምቾት የሚጨምር፣ የቢዝነስ እንቅስቃሴ እና የአገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ምህዳር በመፍጠር #ዲጂታል_ኢትየጵያን እውን ማድረጋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን።

አዲስ ፍጥነት፣ አዲስ ምቾት፣ አዲስ አኗኗር!

ለበለጠ መረጃ: https://bit.ly/49uT5WX

#ITU #GSMA