#ETHIOPIA
🤝 #Somaliland #RedSea #Port
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ምን አሉ ?
" ... እንኳን የኢትዮጵያ ስብራት ጥገና ቀን በጋራ አደረሰን፤ አደረሳችሁ።
በተደጋጋሚ ለህዝባችን ቃል በገባነው መሰረት ኢትዮጵያ ካሏት ዋና ዋና ስብራቶች መካከል አንዱ የሆነው ቀይ ባህርን #access የማድረግ በዛውም #የማልማት ፍላጎት ከሶማሌላንድ ወንድሞቻችን ጋር በተደረገው የትብብር ስምምነት ዛሬ የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራርመናል።
ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ እንዳነሳነው እኛ ያሉንን ሃብቶች የመጋራት ፣ የመካፈልና በጋራ የመልማት ፍላጎት እንጂ ማንንም በኃይል የማስገደድ ፍላጎት የለንም ስንል የነበረው ሃሳብ በተግባር ዛሬ በአዲሱ ዓመት የመጀመሪያው ቀን ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ፣ የሶማሌላንድ ህዝብና ለሰላም ወዳድ ህዝብ ለልማት ወዳድ ህዝብ የምናበስረው የምስራች ይሆናል።
ስብራቶቻችን ይጠገናሉ፣ ኢትዮጵያ ትበለፅጋለች። በገባነው ቃል መሰረት ሀገራችንን ወደሚቀጥለው ደረጃ እናሸጋግራለን።
ስለሆነው ሁሉ ያደረገልንን ፈጣሪን እናመሰግናለን። "
@tikvahethiopia