#ኮንታ

" እናትን ጨምሮ ሁለት ልጆች ህይወታቸውን አጥተዋል "

በመሬት መንሸራተት አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ።

በኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ በኦፓላሸ ቀበሌ በግምት በሊቱ 9 ሰዓት አካባቢ በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት ማለፉን የዞኑ ኮሚኒኬሽን አሳውቋል።

የመሬት መምሸራረት አደጋው ሰሞኑን የጣለ ከባድ ዝናብ ተከትሎ እንደደረሰ የተነገረ ሲሆን በአደጋው እናትን ጨምሮ ሁለት ልጆች ህይወታቸውን አጥተዋል።

ሟቾች የ11ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው ተማሪ አግኔ አሉላ፣ ታናሽ ወንድሟና የ6ኛ ክፍል ተማሪ አማኑኤል አሉላ እና እናታቸው ወ/ሮ ዳምአሌ ደስታ ናቸው።

በደረሰው አደጋ ከሟቾች በተጨማሪ በኦፓ ላሸ እና በኮዳ ማጂ ቀበሌ 25 አባዎራዎችና 175 የቤተሰብ አባላት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በቀበሌ ውስጥ ተጠልለው እንደሚገኙ እንደሚገኙ ተረጋግጧል።

በአደጋው አምስት የቤት እንስሳት መሞታቸውንና በ5 ነጥብ 5 ሄክታር ማሳ ላይ የነበረ ሰብል መውደሙም ተጠቁሟል

የዚህ መረጃ ባለቤት የኮንታ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

@tikvahethiopia