TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ " መንግስት የማያውቀው ፤ የህዝብ ሃብት በማባከን ከቀበሌ እስከ ዞን ስብሰባ መጥራት ምክንያቱ ግልፅ አይደለም " - አቶ ጌታቸው ረዳ በትግራይ የተጀመረው ህግ የማስከበር እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ገለፁ። ፕረዚደንቱ ዛሬ ጥቅምት 16 /2016 ዓ.ም በፅህፈት ቤታቸው በኩል ባወጡት መግለጫ ፤ " የተሰው ታጋዮች መርዶ በተነገረበት…
#ትግራይ

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት አቶ ጌታቸው ረዳ በፅሁፍና ለትግራይ ቴሌቪዥን በድምፅ በሰጡት መግለጫ ፤ " ለነገና እና ለነገ በስቲያ (ጥቅምት 17 እና 18 /2016 ዓ.ም) የሚካሄድ የካድሬ ስብሰባ የለም ፤ የተጠራውም ህጋዊ አይደለም " ብለዋል።

የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በበኩላቸው ለቅዳሜና እሁድ የተጠራው የካድሬዎች ሰብሰባ እንደሚካሄድ በፃፉት ደብዳቤ አስታውቀዋል።

ብዙዎች በጊዚያዊ አስተዳደሩና በህወሓት መካከል እየተፈጠረ ያለው ልዩነት እንዳሳሰባቸው ሰጋታቸው  በመግለፅ ላይ ይገኛሉ።

" ልዩነቱ ወዴት ያመራ ይሆን ? " ብለው በመጠየቅ ላይም እንደሚገኙ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።

@tikvahethiopia