TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል " ም/ቤት መሥራች ጉባዔ በመጪው ዓርብ ነሐሴ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በወልቂጤ ከተማ እንደሚካሄድ ተነግሯል። ክልሉ ካቀፋቸው ከአምስቱ ዞኖች ፦ - ከከምባታ ጠምባሮ፣ - ከሀዲያ፣ - ከጉራጌ፣ - ከስልጤ - ከሀላባ ዞኖች እንዲሁም ከየም ልዩ ወረዳ የተወከሉ የክልል ም/ቤት አባላት ለስብሰባው ሐሙስ ወልቂጤ ገብተው እንዲያድሩ ጥሪ ተላልፏል። በአርቡ ጉባኤ…
#Wolkite

የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የ " ማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል " መስራች ጉባኤ ለማካሄድ የቅድመ ዝግጅት ስራ ማጠናቀቁን አሳውቋል።

በሰባት የክልል ማእከላት እየተደራጀ ያለው የ " ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል " ነሀሴ13 /2015 ዓ/ም በጉራጌ ዞን፤ በወልቂጤ ከተማ የምስረታ ጉባኤውን እንደሚያካሂድ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ እንዳለ ስጦታው ተናግረዋል።

ከንቲባው ፤ አስተዳደሩ በዚህ ጉባኤ ምክንያት ከ2500 እስከ 3000 እንግዶችን ለመቀበል የሚያስችለውን ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ማጠናቀቁን አመልክተዋል።

ከፀጥታው ጋር በተያያዘ ሁሉም የፀጥታ መዋቅር የዞን ፣ ከተማ ፣ አበሽጌ እና ቀቤና ወረዳ በጋራ በመሆን የከተማውን ሰላም ለማስጠበቅ በጋራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

መረጃው የከተማው ኮሚኒኬሽን ነው።

@tikvahethiopia