TIKVAH-ETHIOPIA
#Amhara እጅግ አስከፊ ከነበረው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ገና ያላገገመው አማራ ክልል ዳግም የግጭት ቀጠና እየሆነ መምጣቱና የፀጥታውም ሁኔታ አሳሳቢ የሆነ ደረጃ ላይ መድረሱ ተገልጿል። በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በ " ፋኖ " የታጠቁ ኃይሎች እና በ " መንግሥት የፀጥታ ኃይሎች " መካከል በተከሰቱ ግጭቶች የሰዎች ህይወት አልፏል፤ ጉዳትም ደርሷል። በተለይ ከጥቂት ወራት ወዲህ " የክልሉና የአማራ…
#NewsAlert

የአማራ ክልል መንግሥት በክልሉ ያጋጠመውን የፀጥታ መደፍረስ ለመቆጣጠር የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ እንዲተገብር ጥያቄ አቀረበ።

የክልሉ መንግሥት ፤ ያጋጠመውን የፀጥታ መደፍረስ በመደበኛው የህግ ማስከበር ስርዓት #ለመቆጣጠር_አዳጋች ሆኖ መገኘቱን ገልጿል።

በዚህም የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ እንዲተገብር ይፋዊ ጥያቄ አቅርቧል።

በክልሉ የተከሰተው የሰላም መደፍረስ በክልሉ ከፍተኛ ሰብዓዊ፤ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ እያደረሰ መሆኑን የክልሉ መንግሥት ገልጿል።

" የተከሰተውን የፀጥታ ችግር በቁጥጥር ስር ለማዋል እስካሁን በክልሉና በፌደራል የፀጥታ ኃይሎች በኩል በርካታ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል " ያለው የአማራ ክልል መንግሥት ፤ " የፀጥታ መደፍረስና ጥቃት ፤ ንፁሃን ዜጎች ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳት በአስቸኳይ ለማስቆም የፌደራል መንግስት ከመደበኛው ህግ የማስከበር ስርዓት ባሻገር በኢፌዴሪ ህገ መንግስት መሰረት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ በአፋጣኝ እንዲተገበር " ሲል ጥይቄ አቅርቧል።

" ክልሉ ወደ ቀደመው መረጋጋቱ እንዲመለስ ፤ ዜጎች ሰላማቸው ተመልሶ አርሶአደሩ ወደ እርሻው ክልሉም ወደ ልማት ስራዎች ፊቱን እንዲያዞር ለማድረግ መንግስት ያለበትን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጣ ይገባል " በሚል የአማራ ክልል መንግሥት የፌደራል መንግስትን መጠየቁ ተነግሯል።

@tikvahethiopia